የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በድሬዳዋ ወደ ማምረት በተሸጋገሩ አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎች በተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ሆነናል-ወጣቶች

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፣ ነሐሴ 7/2018(ኢዜአ) በድሬዳዋ በ''ኢትዮጵያ ታምርት'' ንቅናቄ ወደ ማምረት በተሸጋገሩ አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎች በተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ወጣቶች ገለጹ።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታዩ የአሰራር ማነቆዎችን በመፍታት የአገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለማሳደግ ዘመናዊ እና ውጤታማ ምህዳር መፍጠር አስችሏል።

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ንቅናቄው አምራቾች በሙሉ አቅማቸው እንዲያመርቱ ለማስቻል፣ የኃይል፣ የፋይናንስ፣ የመሬት እና የግብዓት አቅርቦት ጥያቄያቸውን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ፈጣን ምላሽ እንዲያገኝ አድርጓል።

ይህም በርካታ አዳዲስና ነባር ፋብሪካዎች ግንባታቸውንና ማስፋፊያቸውን በፍጥነት አጠናቀው ወደ ምርት እንዲሸጋገሩ ያስቻለ ሲሆን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን ማዳን አስችሏል።

እንዲሁም ለበርካታ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች፣ ቋሚና አስተማማኝ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦን አበርክቷል።

አስተየየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ወጣቶችም፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ድጋፍ እና ክትትል ወደ ማምረት በገቡ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች በተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች መካከል ወጣት አሸናፊ አስናቀ እና ወጣት ዱርሲቱ ሁሴን፤ በተፈጠረላቸው የስራ ዕድል ተጠቅመው ህይወታቸውን እየለወጡና ተጨማሪ ትምህርት እየተማሩ መሆኑን አንስተዋል።

በኡርጂ ሳሙና ፋብሪካ በማሽን ኦፕሬተርነት ተቀጥረው የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደቻሉ የተናገሩት ደግሞ ወጣት ኤሊያስ ሐሰን እና ወጣት ኢብሳ አሊ ናቸው።

የፋብሪካ ባለቤቶችና የስራ አመራሮች በበኩላቸው ፋብሪካዎቹ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገቡ ተጨማሪ የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል።

የአሜን የካርቶን ፋብሪካ ባለቤት አቶ ብሩክ በቀለ በበኩላቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ ባደረገላቸው ድጋፍ በ62 ሚሊዮን ብር ካፒታል በአንድ ዓመት ግንባታ አጠናቀው ማምረት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

የፋብሪካው ወደ ስራ መግባት ለ27 ሰዎች ቋሚ የስራ ዕድል በመፍጠሩና ከውጭ የሚገባን ምርት ማስቀረቱን ጠቁመዋል።

የፋብሪካው ምርት ጥራቱን የጠበቀ ከመሆኑም በላይ ከፕላስቲክ የጸዳች ድሬዳዋን ለመፍጠር የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኡርጂ ሳሙና ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሐምዲያ ዑመር በበኩላቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ለፕሮጀክት ማስፋፊያ መሬት፣ ለፋይናንስ እና ለኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት ጥያቄቸው ፈጣን ምላሽ እንደሰጣቸው ተናግረዋል።

ይህም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ግንባታቸውን አጠናቀው ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ ማስቻሉን ገልጸው ለ46 ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም አስረድተዋል።

የተለያዩ የውሃ ማጠራቀሚያ (ሮቶ) ምርቶቹን ወደ ጅቡቲ እና ሀርጌሳ ከተሞች በመላክ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ያለው አሽራፍ የፕላስቲክ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ንጉሴ ፋብሪካው ለ40 ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

አስተዳደሩ ለማምረቻ ቦታ ጥያቄያቸው ፈጣን ምላሽ በመስጠቱ በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት እንደተነሳሱም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026