የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በመኸር እርሻ ከ500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በመኸር እርሻ ከ500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና በመምሪያ ገለጸ።

በዞኑ በ2018/2019 የምርት ዘመን ከ586 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር በመሸፈን ምርታማነትን ለማሳደግ ግብ

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ንጉሤ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ የተሻሻሉ አሠራሮችና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም 501 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር መሸፈን ተችሏል።


በዘር ከተሸፈነው መሬት ውስጥ በቆሎ፣ ገብስ፣ ስንዴ፣ ጤፍና ሰሊጥ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዘሮች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።

በምርት ዘመኑ የመካናይዜሽን እርሻን በማስፋፋት በትራክተር ለማረስ ከታቀደው ከ71 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ እስካሁን 94 በመቶውን ማሳካት መቻሉንም ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በምርት ዘመኑ ለማልማት ከታቀደው መሬት ከ24 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅት ለምርት ዘመኑ ከቀረበው ከ627 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 403 ሺህ ኩንታሉ ለአርሶ አደሮች ተሰራጭቶ ጥቅም ላይ መዋሉን አመልክተዋል።

ዝናብ ዘግይቶ መጣል በጀመረባቸው አካባቢዎች የተገኝውን እርጥበትን በመጠቀም በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ሰብሎችን አርሶ አደሩ ለይቶ እንዲያለማ ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

በዞኑ ጠገዴ ወረዳ በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ሽባባው መሪድ በበኩላቸው፤ የመካናይዜሽን እርሻን በመጠቀም ከ500 ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈናቸውን ተናግረዋል።

መሬቱን ያለሙት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው አኩሪ አተር፣ ጥጥ፣ ሰሊጥና ማሽላ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስከ 8 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎችም ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

የሰው ጉልበትን በዘመናዊ የእርሻ ትራክተር በመተካት የሰብል ምርታማነታቸውን ማሳደጋቸውን የገለጹት ደግሞ በዚሁ ወረዳ በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ቸሬ ገብሬ ናቸው።

የተረከቡትን 77 ሄክታር መሬት ቀድመው በማለስለስ በጥጥና በአኩሪ አተር ሰብሎች ሸፍነው እያለሙ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በዞኑ በ2017/2018 የምርት ዘመን ከለማው 552 ሺህ 895 ሄክታር መሬት 18 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026