የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ነሐሴ 8/2018(ኢዜአ )፡- በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ መሆናቸውን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለፁ።

በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በአዳማ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል መሰረተ ልማትና ሌሎች የልማት ስራዎችን ገብኝቷል።


በዚህ ወቅት አቶ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት፤ በከተሞች በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ እየታዩ ያሉ ለውጦች በዘርፉ የተሻለ ልምድና ዕውቀት እየተገነባ ለመሆኑ ማሳያ ናቸው።

"ከዚህ ቀደም ልምድ ለመቅሰም ወደ ውጭ ሀገር ከተሞች እንሄድ ነበር፤ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ግን በሀገር ውስጥ ከተሞች ከቴክኖሎጂ ልማትና አጠቃቀም፣ ከአገልግሎት ዲጂታላይዜሽንና መሠረተ ልማት ዝርጋታ አንጻር ልምድና ዕውቀት መቅሰም እየቻልን ነው" ብለዋል።

በተለይ በአዳማ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን እና የጸጥታና ደኅንነት አሠራሮችን ዘመናዊ ከማድረግ አኳያ የተሰሩ ሥራዎች ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው እንደሁኑ ገልጸዋል።

በተመሳሳይም በትራንስፖርት ስምሪትና በትራፊክ ቁጥጥር ሥርዓት፣ ቴክኖሎጂን በማላመድና አገልግሎት ላይ በስፋት በማዋል ረገድ ጥሩ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።


በተለይ የመሬት ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና ለሕዝብ ልማት በማዋል ረገድ የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሬት ካዳስተር ሥርዓት በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

በከተማ ግብርና፣ የአርሶ አደሩን ሕይወትና የአኗኗር ዘይቤ ለማዘመንና ከተማዋ አርሶ አደሩን በማቀፍ ዕድገቷ እንዲቀጥል የአርሶ አደሮች ሞዴል መንደር ልምድ የተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም አርሶ አደሩ የተሟላ መሠረተ ልማት በአንድ ቦታ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ከንቲባው አክለውም ከአዳማ ከተማ የተገኘውን ተሞክሮ በከተማቸው ካለው አተገባበር ጋር በማቀናጀት ወደ ውጤት እንደሚቀይሩትም ተናግረዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፤ በከተማዋ በተከናወነው የመሠረተ ልማት ዝርጋታና አገልግሎትን በማዘመናችን አዳማ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንድትሆን ሰፊ ዕድል እየፈጠረ ነው ብለዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመንና በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ መቻሉንም ገልጸዋል።

በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ለማዘመን የተሠራው ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም የመሬት ሀብቱን በአግባቡ በማስተዳደር ከሌብነትና ምዝበራ መታደግ መቻሉን፣ የከተማዋ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን፣ ሕዝቡ በከተማዋ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ እንዲጨምርና እንዲጠናከር ማስቻሉንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026