የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ነሐሴ 9/2018(ኢዜአ):- የእንስሳት ሃብት ህገ-ወጥ ንግድን ለመከላከልና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን የቀይ አፈር-የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ግንባታ በመገባደድ ላይ ሲሆን በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል ተብሏል።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊና ንግድና ገበያ ልማት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ፍቅርተ አብርሃም፤ በክልሉ ያለው ሰፊ የእንስሳት ሃብት ልማት ለዜጎች የተሻለ ጥቅም እንዲሰጥ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በእንስሳት ሃብት ላይ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ ንግድ ለመከላከልና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል።

የቁም እንስሳትን ወደ ግብይት ማዕከላት በማቅረብ በተሻለ ዋጋ ለማህበራትና ለዩኒየኖች ለማቅረብ የሚያስችል አሰራር ስለመዘርጋቱ አንስተዋል።

በኤክስፖርት እንስሳት ማሰባሰቢያ ማዕከላት አማካኝነት በሀገሪቱ ለሚገኙ የኤክስፖርት ቄራዎች ዩኒየኖች በቀጥታ የሚያቀርቡበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።


በክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ የአርብቶ አደር አደጋ ስጋት ቅነሳና አካታች የኢኮኖሚ እሴት ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ስዩም መታፈሪያ (ዶ/ር)፤ የእንስሳት ሀብት በብዛት በሚገኝባቸው የክልሉ አካባቢዎች የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከላት እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከላት የኤክስፖርት ስታንዳርዱን የጠበቁ እንስሳትን ማቅረብ በሚያስችል መልኩ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይም የኤክስፖርት ቄራዎችን እና የተቀባይ አገራትን ፍላጎት ያማከለ የቁም እንስሳት በብዛትና በጥራት በማቅረብ ሀገሪቱ ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ እንድታገኝ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


የቱርሚ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሀማ አይኬ፤ በከተማ አስተዳደሩ የተገነባው የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል በተለይም አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል ሲሉ ተናግረዋል።

የቁም እንስሳት ንግድ ህጋዊ ስርአቱን የተከተለ ሲሆን የመንግስት የገቢ ምንጭ እንደሚሆንና በከተማው ለሚገነቡ መሰረተ ልማቶች መሳለጥም ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል።

በቅርቡ ግንባታው ተጠናቆ የተመረቀው የኤክስፖርት እንስሳት ማሰባሰቢያ ማዕከል ኢትዮጵያ ከእንስሳት ሀብቷ ተገቢውን ጥቅም የምታገኝበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026