የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምዕራብ ጎንደር ዞን ከ172 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥና ማሾ ሰብል ለምቷል

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳ ውኃ፣ ነሐሴ10/2018 (ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በመኸር እርሻ ከ172 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የሰሊጥና ማሾ ሰብሎችን ማልማት መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

​የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ ለወጪ ንግድና ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ የግብርና ምርቶችን በማምረት ላይ ይገኛል።

በዚህም እስካሁን በተደረገው ጥረት በአጠቃላይ በሰሊጥና በማሾ ሰብል ከለማው ከ172 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በሰሊጥ፣ ቀሪው ደግሞ በማሾ ሰብል መሸፈኑን ተናግረዋል።


ከዚህ ልማትም ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል።

ምርታማነቱን ለማሳደግም ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘርና የመካናይዜሽን አስተራረስ ዘዴዎችን በመጠቀም መዝራት መቻሉን ጠቁመዋል።

በሰብል ልማቱ ከ59 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና 500 የሚደርሱ ባለሀብቶች እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸው፣ የአረምና የተባይ መከላከል ተግባራት በቅንጅት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለገበያ ለማቅረብም በቅድመና ድህረ-ምርት አያያዝ ላይ ተገቢው ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ አብራርተዋል።

በዞኑ የመተማ ወረዳ አርሶ አደር አቶ መሐመድ አህመድ በበኩላቸው፣ ዝናብ ዘግይቶ ቢጥልም የተገኘውን እርጥበት በመጠቀም አራት ሄክታር መሬታቸውን በሰሊጥ መሸፈናቸውን ተናግረዋል።

በኩታ ገጠም አስተራረስና በዘመናዊ መካናይዜሽን ተጠቅመው ካለሙት ሰብልም ከ30 ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

ሌላው የመተማ ወረዳ አርሶ አደር ደሳለኝ ገብሬ፣ በዘንድሮው የመኸር እርሻ የግብዓት አቅርቦት በወቅቱ መድረሱ ማሾና ሰሊጥን በስፋት ለማልማት መቻላቸውን ገልጸዋል።

አሁንም ዋና ትኩረታቸው ሰብሉን ከተባይ መጠበቅና ምርቱን ከብክነት በጸዳ መልኩ ሰብስቦ ለገበያ ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል።

በዞኑ ባለፈው የምርት ዘመን ከ163 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል ለምቶ ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026

የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...

Jul 9, 2026