
ሆሳዕና፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የዘርፉን ዕድገት የሚመጥን ብቃት እንዲኖራቸው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ከክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ጋር በመቀናጀት የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ብቃት ማረጋገጫ አሰጣጥ ላይ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኑሪ ከድር በዚህ ወቅት እንዳሉት ክልሉን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በተሰሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል።
ውጤቶቹን ለማስቀጠል በክልሉ የሚገኙ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወቅቱን የዋጀና የዘርፉን ዕድገት የሚመጥን ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ ገልጸው፣ ተቋማቱን የማብቃትና የማጠናከር ሥራ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በክልሉ በሆቴል ኢንቨስትመንትና በሌሎች የዘርፉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የሚታየውን ውስንነት ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን ተናግረው፣ የዛሬው የምክክር መድረክም የእዚሁ አካል መሆኑን አመልክተዋል።
እንደ አቶ ኑሪ ገለጻ፣ ተቋማቱ ለቱሪስቶች የተሟላ አገልግሎት ከማቅረብ አኳያ ውስንነት እንዳለባቸው በተደረገ ድጋፍና ክትትል ተለይቷል።
ውስንነቶችን ለመፍታት እንደሚሰራ ገልጸው በተለይ ከፍተኛ ድርሻ ያለው የሆቴል አገልግሎት ዘርፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የአገልግሎት አሰጣጥ ብቃት ማረጋገጫ እንዲያሟሉ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱንም አስታውቀዋል።
የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሻድ በበኩላቸው፣ ቢሮው በንግዱ ዘርፍ የማህበረሰቡን ደህንነት ለማስጠበቅ የወጣውን አዋጅ ለማስተግበር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ከሆቴል አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ በርካታ ችግሮች እንዳሉ ጠቁመው፣ ችግሮቹን ለመፍታት የድጋፍና ክትትል ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑንም አመልክተዋል።
ተቋማቱ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉና ለዘርፉ መዘመንና ዕድገት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ህጋዊ መሰረት ኖሯቸው እንዲንቀሳቀሱ የማድረግ ስራም ይሰራል ብለዋል፡፡
በጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የቱሪዝም አገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ የሥራ ሂደት ቡድን መሪ ወይዘሮ ወይንሸት ሰተቱ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በዞኑ በቱሪስት መዳረሻዎች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ ነው።

ይህም የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ይረዳል ያሉት ቡድን መሪዋ፣ ለስኬቱም በሆቴሎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን የማሻሻልና የማብቃት ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የማረምና የማስተካከል ሥራዎች እንደሚከናውኑም ገልፀዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የዞንና የልዩ ወረዳ የባህል ቱሪዝም እና የንግድና ገበያ ልማት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026