የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሲዳማ ክልል ስምንት ከተሞች የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው

Jul 31, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል በስምንት ከተሞች የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡

በክልሉ የተለያዩ ከተሞች ያሉ ነዋሪዎች በበኩላቸው የኮሪደር ልማት ሥራው ከተሞችን ምቹና ተመራጭ ከማድረግ ባለፈ ለዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ እያገለገሉ በመሆኑ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

የቢሮ ሃላፊው አቶ አሻግሬ ጀምበሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ እንደሀገር የተጀመረው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ለነዋሪዎችና ለኢንቨስትመነት ተመራጭ እያደረገና ዕድገታቸውን እያፋጠነ ነው፡፡

በአሁኑ ወቅትም በሲዳማ ክልል በስምንት የተለያዩ ከተሞች ከ28 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዚህም ሀዋሳን ጨምሮ ይርጋለም፣ ወንዶገነት፣ ዳዬ፣ አለታ ጩኮ፣ አለታ ወንዶ፣ ለኩና ይርባ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አቶ አሻግሬ ገልጸዋል፡፡

በሀዋሳ ከተማ ብቻ ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ አሻግሬ፣ የኮሪደር አካል የሆነው ከስምንት ኪሎ ሜትር በላይ የአስፓልት መንገድ ግንባታም እየተፋጠነ መሆኑን አስረድተዋል።

በከተሞቹ የኮሪደር ልማት ሥራው እየተፋጠነ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው፣ ሥራውን በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።


የኮሪደር ልማቱ የከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በማሳለጥና ማህበራዊ ችግሮችን እየፈታ በመሆኑ ህብረተሰቡ በተለያየ መንገድ ተሳትፎውን እያሳደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

"የኮሪደር ልማት ሥራው በክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት እየተመራ ነው" ያሉት አቶ አሻግሬ፣ ድጋፍና ክትትልን ጨምሮ ተሞክሮ በመቀመር ስራውን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኮሪደር ልማቱ ስማርት ሲቲን ለመገንባት የተጀመረውን ጥረት በሚያግዝ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸው፣ ለስኬታማነቱ ተቋማት በቅንጅት እንዲሰሩ የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል።


በክልሉ የይርጋለም ከተማ ነዋሪው አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለከተሞች በተሰጠው ልዩ ትኩረት በከተማቸውም የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንና ገጽታዋም እየተቀየረ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተማዋ ረዥም እድሜን ብታስቆጥርም የእድሜዋን ያህል በልማት እንዳልገፋች አስታውሰው በከተማው እየተከናወነ ባለው የልማት ሥራ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡


በወንዶገነት ከተማ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ እየተከናወነ ያለው የመሰረተ ልማት ሥራ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ አቶ መሳፍንት በራሶ ናቸው፡፡

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026