የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ በፍራፍሬ ልማት የተገኘውን ውጤት የበለጠ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምት ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በፍራፍሬ ልማት የተገኘውን ውጤት የበለጠ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በውስጥ አቅም ለመሸፈን በመቻሉ ለበልግ እርሻ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል

በጽሕፈት ቤቱ የቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ ቡድን መሪ አቶ አሰፋ መኮንን ፤ በዞኑ ለፍራፍሬ ልማት የሚመች የግብርና መሬት እንዳለ ለኢዜአ ገልጸዋል።

በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለልማቱ በተሰጠው ትኩረት የፍራፍሬ ልማት ሥራ በስፋት እየተተገበረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ለዚህም የዞኑ አርሶ አደሮች ከመደበኛ የሰብል ልማት በተጓዳኝ አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ እና ሌሎችንም የተመረጡ የፍራፍሬ ዓይነቶች እንዲያለሙ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።


በዞኑ ያለውን ምቹ ሥነ-ምህዳር፣ የአየር ንብረት እና በቂ የውኃ ሀብት በመጠቀም እስካሁን 15 ሺህ 371 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ማልማት መቻሉን አስታውቀዋል።

የፍራፍሬ ምርት እየለማበት ከሚገኘው ሄክታር መሬት ውስጥ ከፊሉ ምርት መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ በ2017/2018 ምርት ዘመን ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ መቅረቡን አብራርተዋል።

የፍራፍሬ ምርቱ በአመዛኙ በጉደያ ቢላ፣ ጎቡ ሰዮ፣ ሲቡ ስሬ እና ጉቶ ጊዳ ወረዳዎች የተመረተ ሲሆን፤ የልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች የፍራፍሬ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ገልጸዋል።

የፍራፍሬ ልማቱን ለማስፋፋት የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ ተግባራዊ መደረጉን አንስተው፤ በየደረጃው በሚገኙ ችግኝ ማፍያ ጣቢያዎችም የፍራፍሬ ችግኞች በተደራጀ መልኩ በጥራትና በብዛት እየተዘጋጁ ለልማቱ ተሳታፊዎች ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል።

በምስራቅ ወለጋ ዞን ጎቡ ሰዮ ወረዳ ከልማቱ ተሳታፊዎች መካከል አርሶ አደር ስዒድ ጂላሉ በሰጡት አስተያየት፤ ባላቸው አንድ ሄክታር ይዞታ ላይ አቮካዶና ሙዝ በማልማት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የፍራፍሬ ምርታቸውን ከሀገር ውስጥ ገበያ ባለፈ መንግሥት ባመቻቸላቸው የገበያ ትስስር በመጠቀም ካለፈው ዓመት ወዲህ 33 ኩንታል አቮካዶ ወደ ውጭ ሀገር በመላክ 150 ሺህ ብር ትርፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


ከሙዝ ልማት ጋር በተያያዘም በስፋት ሥራ ውስጥ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ የደረሰ ሙዝ በመሰብሰብ ለገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

ሌላኛው በዞኑ ጉቶ ጊዳ ወረዳ አርሶ አደር ሀብታሙ ደጀኔ በበኩላቸው፤ በየዓመቱ ከሚያመርቱት አቮካዶ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት በሰብል ምርት ላይ ብቻ በመሰማራት የሚያገኙት ገቢ ውስን እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ባገኙት ምርጥ ዘር እና ድጋፍ በመጠቀም ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህ ዓመት በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ 20 ኩንታል አቮካዶ ምርት በመሰብሰብ ለገበያ ማቅረባቸውን አውስተዋል።

እንደ አርሶ አደሮቹ ገለጻ የአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት የተሻለ ገቢ ከማስገኘት ባለፈ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሥርዓተ ምግብ ለማሻሻል አስችሏቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026