የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በነዳጅ አቅርቦት ዙሪያ በሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018(ኢዜአ) ፦ በነዳጅ አቅርቦት ዙሪያ በሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

በነዳጅ ስርጭትና ግብይት ሂደት ላይ የሚታዩ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር በስድስት ክልሎችና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች የተጀመረው የተቀናጀ ዘመቻ መጠነ ሰፊ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገልጸዋል።


ባለፉት ቀናት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥርም የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ኢዜአ ከሚኒስቴሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በዚህ መሰረትም በሕገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ 250 ሺህ 221 ሊትር ቤንዚን እና 198 ሺህ 432 ሊትር ናፍጣ ተይዞ መወረሱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ከተወረሰው ነዳጅ መካከል በሽያጭ ለጥቅም እንዲውል ከተደረገው ውስጥ ከ48 ሚሊዮን 663 ሺህ ብር በላይ ለመንግሥት ገቢ መሆኑን ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በአሻጥሩ ተሳትፈው የተገኙ 613 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።

ከተያዙት ግለሰቦች መካከል የንግድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች፣ የሬጉላቶሪ ባለሙያዎች፣ የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችና ሠራተኞች እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ አካላት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።


እርምጃው በታችኛው መዋቅር ላይ ብቻ ሳይሆን በውሳኔ ሰጪዎች ላይም ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸው ይህ የተቀናጀ የቁጥጥር ሥራ በዘርፉ የሚታየውን አሻጥር በመቅረፍ ፍትሃዊ የነዳጅ ስርጭት እንዲኖር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

ያለውን ዓለም አቀፋዊ የነዳጅ ገበያ ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ነዳጅ አከፋፋዮችና ህብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙም ሚኒስትሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Ethiopian News Agency #ኢዜአ #ነዳጅ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026