🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአረንጓዴና የታዳሽ ኃይል ልማትን የሚያበረታታ የተሟላ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረጓ በቀጣናው ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እንዳደረጋት ተገለጸ።
በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም የፖሊሲ ጥናት ማዕከል ኃላፊና በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አማካሪ አሊ ዛፋር፤ የሀገሪቱ የኃይል አቅርቦት ምንጭ የሆነው ታዳሽ ኃይል መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ከውኃ ሀብት የሚመነጨው ኃይል የኢንዱስትሪ ልማትን በማሳለጥ ሀገራዊ የልማት ግቦችን በማሳካት ኢትዮጵያን ከቀጣናው ሀገራት ጋር በኃይል ያስተሳስራል ሲሉም ለኢዜአ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባደረገችው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የዋጋ ግሽበት መቀነሱንና የውጭ ምንዛሬ ክምችት መሻሻሉን አንስተዋል።

በቀጣናው ዝቅተኛ የኃይል አቅርቦት ዋጋ ያላት፣ ለኢንቨስትመንት ምቹ እና መንግሥት ለዘርፉ ከፍተኛ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳራሻ እንዳደረጋትም አመላክተዋል።
ሀገሪቱ ያላትን የኢንቨስትመንት ዕድሎች ለማስተዋወቅ የምታደርገውን ጥረት በመጥቀስ፤ መንግሥት በታዳሽ ኃይል የሚመራ አረንጓዴ ልማትን ለማረጋገጥ ያለውን ጽኑ አቋም አድንቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ትልቅ ትኩረት በመስጠት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንዲበረታቱ እያደረገች መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በአካባቢ ጥበቃና በታዳሽ ኃይል ልማት ግንባር ቀደም መሆኗን ጠቅሰው፤ ሌሎች ሀገራት ሊማሩበት የሚገባ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026