የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመረጃ አያያዝና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋይ እርካታን እያሳደገ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሚያዚያ 12/2018(ኢዜአ)፡-የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመረጃ አያያዝና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋይን እርካታ ማሳደጉ ተገለጸ።

"ዲጂታል ኢትዮጵያ" ተግባራዊ እያደረጉ ካሉ የመንግስት ተቋማት መካከል አንዱ የፍትህ ተቋማት ተጠቃሽ ናቸው።

በዚህ ረገድ የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመረጃ አያያዙንና አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው በቪዲዮ ኮንፈረንስ ጭምር ችሎት የሚከታተሉበትን አሰራርን እየተገበረ ይገኛል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ የጅማ ዞን ከፍተኛ የፍርድ ቤት ተገልጋዮችና ፕሬዚዳንቱን አነጋግሯል።

ከፍርድ ቤቱ ተገልጋዮች መካከል በጅማ ዞን ማና ወረዳ ነዋሪ አቶ ጀዋር አባራያ የፍትህ ሂደቱን ለመከታተል የቪዲዮ ኮንፈረንስና ዲጂታል አሰራሮች መተግበራቸው ፍትህ ለማግኘት እስከ ጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ድረስ በመጓዝ ያወጡት የነበረውን ወጪ እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል።

በዞኑ የነዲ ጊቤ ወረዳ ነዋሪ ሚስባሂ ሼህ ኢማም በበኩላቸው እንዳሉት የፍርድ ቤቱ ዲጂታላይዝድ አገልግሎት አሰጣጥ ከመደበኛ ሥራቸው ሳይነጠሉ ባሉበት ሆነው ፈጣን ፍትህ ለማግኘት አስችሏቸዋል።

የፍርድ ቤቱ ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ መረጃዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማግኘት የሚያስችልና ሥራን የሚያሳልጥ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የህግ ባለሙያ እና ጠበቃ ታደለች ዲባዩ ናቸው።


የፍትህ አገልግሎቱ ዲጂታላይዝድ መደረግ ለተገልጋዩም ሆነ ለህግ ባለሞያዎች እፎይታ ሰጥቷል ብለዋል።

"በወረዳ ላይ ላልተፈቱ ችግሮች ተገልጋዮች ወደ ጅማ ከተማ መምጣት አይጠበቅባቸውም" ያሉት ደግሞ የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ታጁ ሸሪፍ ናቸው።

ዘመናዊ አሰራሩ ተገልጋዮች አቤቱታቸውን በኢ-ፋይል ልከው ባሉበት ቀርበው የመከራከር ወይም ጉዳያቸውን የመከታተል እድልን ያሰፋ ነው ብለዋል።

አገልግሎቱ ከወረቀት ንክኪ በጸዳ መልኩ መሰጠቱ አገልግሎቱን ከማቀላጠፍ ባለፈ የመረጃ ግልጽነትን ለመፍጠር ማገዙን ጠቁመዋል።


የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቶፊቅ ሸምሱ በበኩላቸው፣ ዞኑ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ተደራሽነትን እውን ለማድረግ የተለያዩ መተግበሪያዎች መበልጸጋቸውን ገልጸዋል።

ችሎቶች ጥራቱን በጠበቀ የቪዲዮ ኮንፈረንስ እየተካሄዱ መሆናቸውን ጠቅሰው ለክስ፣ ለይግባኝና መሰል አገልግሎቶች ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት መምጣት ሳያስፈልግ በወረዳ እና በክላስተር ቀበሌዎች ሆነው መከታተል እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በተጨማሪም በዞኑ 19 ወረዳዎች በዐቃቤ ህግ እና በፍርድ ቤት መካከል የወረቀት ንክኪ ሳይኖር በዲጂታል መንገድ ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በቀጣይም የፍትህ ስርዓቱን የሚያሳልጡ አገልግሎቶችን በሁሉም ወረዳዎች በማዳረስ "ዲጂታል ኢትዮጵያን" እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026