የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ገለጹ፡፡

የአውሮፓ ሕብረት እና ኢትዮጵያ የቢዝነስ ፎረም "ዓለም አቀፍ የገበያ መግቢያ አቅምን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ዘላቂ ዕድገት ማስመዝገብ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ሪፎርም አድርጋለች።

ኢትዮጵያ አካታችና ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማድረግ ያላትን ዕምቅ አቅም መጠቀም የሚያስችል ለውጥ እያመጣች መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያና የአውሮፓ ሕብረት ቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለማውጣት፣ ትብብርን ለመፍጠር፣ የገበያ አማራጮችን ለማሰስ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ የግሉን ዘርፍ በማጠናከር ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንትን መሳብ መቻሉንም ገልጸዋል፡፡

ከሪፎርሙ በኋላ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ጨምሯል፤ የዋጋ ግሽበት ቀንሷል፤ ከወጪ ንግድ የሚገኘው የምንዛሪ መጠን በእጅጉ አድጓልም ብለዋል።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም በተያዘው ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘገብ መተንበዩን በመጥቀስ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን እያጠናከረች መሆኑን ገልጸዋል።


መንግሥት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎና የዲጂታል ግብይትን ማጠናከር የሚያስችል የዲጂታል ክፍያና አገልግሎት ስርዓት ማዘመኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በብዝሀ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ተመራጭ መሆኗን በመጥቀስ፣ የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በታዳሽ ሀይል፣ ቴክኖሎጂ፣ ጋርመንትና መሰል ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ ብለዋል።

ለኢንቨስትመንት ምቹ ሥነ ምህዳርና መሰረተ ልማት በመዘርጋት ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን ገልጸዋል።

የአውሮፓ ሕብረትና አባል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚችሉ ገልጸው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ለኢንቨስተሮች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው ብለዋል።

የኦስትሪያ ሪፐብሊክ የአውሮፓና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሚኒስትር ቤአተ ማይነል ረይዚንገር ፤የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጠንካራ የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር የሚፈጠርበት ወቅት መሆኑን ገልጸዋል፡፡


የዓለም ጂኦፖለቲካና ፖሊቲካዊ ሁኔታ ፈታኝ መሆኑን ገልጸው፤ ኦስትሪያ የዓለምን ንግድና ኢንቨስትመንት በር ክፍት ለማድረግ በሚደረገው ጥረት አጋር ለመሆን ዝግጁ ናት ብለዋል፡፡

በኦስትሪያ የኢንዱስትሪ አቅሞችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ ከጣሊያን ጋር በመተባበር ለአየር ንብረት ለውጥ በማይበገር የቡና ምርት የዓለም አቀፍ መግቢያ ፕሮጀክት እየተሳተፉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዓለም ልዩ የሆነ የቡና ሥርዓት ዝግጅት እንዳላት ገልጸው፤ በኢ-ተገማች የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ከአጋራ አካላት ጋር ትብብርን ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተስፋ ያላት ሀገር ናት ያሉት ሚኒስትሯ፤ የኦስትሪያና አውሮፓ ህብረት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026