የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የህብረት ስራ ማህበራት ለኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት ናቸው

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦የህብረት ስራ ማህበራት የተቀላጠፈ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ፤ የካፒታል መጠንን ለመጨመር እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት መሆናቸውንየቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሬትና ህብረት ስራ ማደራጃ ቢሮ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ 2ኛውን ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ በአሶሳ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሬትና ህብረት ስራ ማደራጃ ቢሮ ኃላፊ አቶ ካሚል ሀመድ፤ የህብረት ስራ ማህበራት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ብዝሃ ኢኮኖሚን መሠረት ያደረገ ሪፎርም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የህብረት ስራ ማህበራት የተቀላጠፈ ግብይት እንዲኖር ለማድረግ የካፒታል መጠንን ለመጨመር እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት መሆናቸውን ገልጸዋል።

ንቅናቄው በክልሉ የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀታቸውን በማዘመንና የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ኢኮኖሚ በማሳደግ ረገድ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን የህብረት ስራ ግብይት መሪ ስራ አስፈጻሚ ንጋቱ ቶላ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ንቅናቄው የህብረት ስራ ማህበራት ተግባር እና ተልዕኳቸውን እንዲወጡ የሚያስችል ነው ብለዋል።


ንቅናቄው የህብረት ስራ ማህበራት ወደ ኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ እንዲሁም በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል እንደሆነ አንስተዋል።

በመጀመሪያው ዙር የንቅናቄ መድረክ ተሳታፊ የነበሩ የህብረት ስራ ማህበራት አመቻቾች በአደረጃጀት ደካማ የነበሩ ማህበራት እንዲጠናከሩ እና በኢኮኖሚ አቅማቸው ጠንካራ እንዲሆኑ ማድረጋቸውን አመልክተዋል።

ለስምንት ቀናት የሚቆየው የንቅናቄ መድረክም በህብረት ሥራ ሪፎርም ፅንሰ-ሐሳቦች እና በዘመናዊ የህብረት ስራ አሠራሮች እንዲሁም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩርም አስታውቀዋል።

በንቅናቄው ላይ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና ከአጎራባች የኦሮሚያ ክልል አራት ዞኖች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026