የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በምርምር በማዳበር የመድኃኒት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት እየተሠራ ነው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 24/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በምርምር በማዳበር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው 5ኛውን ሀገር አቀፍ የጤና ምርምር ሲምፖዚየም አካሂዷል።


በዩኒቨርሲቲው የአሥራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ቴዎድሮስ ክፍለዮሐንስ በዚሁ ወቅት፤ ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ ተግባር ተኮር ምርም እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

በአንኮበር የዕጽዋት የምርምር ጣቢያ በማቋቋም የመድኃኒት አቅርቦትና ሌሎች ዘርፎች ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ሥራ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በጣቢያው ዕጽዋት ለመድኃኒት ቅመማና ክትባት ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ዐቅም ለመፍጠር ከአርማወር ሐሰን የምርምር ኢንስቲትዩትና ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል።


ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተገኙ ውጤቶችን በማዳበር ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን ሂደት ለማሳካት እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።


በአርማወር ሐሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የዕውቀት አስተዳደርና ሥርፀት ዳይሬክተር ዶክተር አክሊሉ ዓለሙ በበኩላቸው፤ ተቋሙ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በመድኃኒትና ክትባት ላይ በማተኮር እየሠራ ይገኛል።

በሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ የተመሰረተ የመድኃኒት አቅርቦት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር እያሱ መስፍን ደግሞ፤ በዘርፉ የምርምር ኮንፈረንስ መዘጋጀቱ የዕውቅትና የልምድ ልውውጥ በማድረግ ችግር ፈች የምርምር ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥልሉ ያደርጋል ነው ያሉት።

ይህም በጤናው ዘርፍ እየተካሄደ የሚገኘውን በሽታን የመከላከልና አክሞ የማዳን አቅጣጫ በሳይንሳዊ ምርምር በማገዝ ውጤማ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026