🔇Unmute
ደብረ ብርሃን፤ ሚያዝያ 24/2018 (ኢዜአ)፡- ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በምርምር በማዳበር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው 5ኛውን ሀገር አቀፍ የጤና ምርምር ሲምፖዚየም አካሂዷል።

በዩኒቨርሲቲው የአሥራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ቴዎድሮስ ክፍለዮሐንስ በዚሁ ወቅት፤ ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ ተግባር ተኮር ምርም እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በአንኮበር የዕጽዋት የምርምር ጣቢያ በማቋቋም የመድኃኒት አቅርቦትና ሌሎች ዘርፎች ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ሥራ እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በጣቢያው ዕጽዋት ለመድኃኒት ቅመማና ክትባት ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ዐቅም ለመፍጠር ከአርማወር ሐሰን የምርምር ኢንስቲትዩትና ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተገኙ ውጤቶችን በማዳበር ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን ሂደት ለማሳካት እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።

በአርማወር ሐሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የዕውቀት አስተዳደርና ሥርፀት ዳይሬክተር ዶክተር አክሊሉ ዓለሙ በበኩላቸው፤ ተቋሙ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በመድኃኒትና ክትባት ላይ በማተኮር እየሠራ ይገኛል።
በሀገር በቀል ዕውቀቶች ላይ የተመሰረተ የመድኃኒት አቅርቦት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር እያሱ መስፍን ደግሞ፤ በዘርፉ የምርምር ኮንፈረንስ መዘጋጀቱ የዕውቅትና የልምድ ልውውጥ በማድረግ ችግር ፈች የምርምር ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥልሉ ያደርጋል ነው ያሉት።
ይህም በጤናው ዘርፍ እየተካሄደ የሚገኘውን በሽታን የመከላከልና አክሞ የማዳን አቅጣጫ በሳይንሳዊ ምርምር በማገዝ ውጤማ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን አስረድተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026