የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረዋል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ ሚያዚያ 24/2018(ኢዜአ)፦ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተወዳዳሪትውልድ በመገንባት ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ተናገሩ።


በአስተዳደሩ ለሶስት ቀናት የተካሄደው የትምህርት ቤቶች የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች አውደ ርዕይ ዛሬ ተጠናቋል።

የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ፤በአውደ ርዕዩ ላይ የቀረቡት የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የተጀመሩ አበረታች ጉዞዎችን ለማሳካት የጎለ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ብለዋል።

በትምህርት ቤቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎትና ጥበብ ያላቸውን ታዳጊ ተማሪዎችን ለማፍራት የሚከናወኑ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

በአውደ ርዕዩ የቀረቡ ችግር ፈቺ የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው፤ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ዕውቀት፣ ክህሎትና ጥበብ የተላበሱ ታዳጊዎችን ለማፍራት የተጀመሩ ጥረቶች ፍሬያማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በአውደ ርዕዩ በየዘርፉ የቀረቡ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች የዚሁ መገለጫ መሆናቸውን በመግለፅ ።

በቀጣይም የፈጠራና የምርምር ስራዎችን በጥራት፣ በስፋት እና በተሻለ ከፍታ ለማሳደግ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና ከድሬዳዋ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ምሁራን ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል ።

የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን የፈጠራ ውጤቶቹን በመገምገም በየዘርፉ የተሻሉትን የፈጠራ ውጤቶች ደረጃ መለየቻቸውም ታውቋል።

በአውደ ርዕዩ ላይ በድሬደዋ አስተዳደር የሚገኙ የ1ኛ እና 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች ናቸው የቀረቡት።

በአውደ ርዕዩ በየዘርፉ የተሻለ የፈጠራ ሃሳቦችን እና ውጤቶችን ይዘው ለቀረቡት ተማሪዎች ሽልማት ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026