የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በብሄረሰብ አስተዳደሩ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የዝናብ አጠር የአየር ጠባይን ተቋቁሞ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የብሄረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ 113 ሚሊየን ብር በጀት መመደቡ ታውቋል።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በብሄረሰብ አስተዳደሩ የመስኖ ተቋማትን በማስፋት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

በዚህም ካሁን ቀደም የተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርሶ አደሩን የግብርና ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል።

ዘንድሮም ተግባሩን ለማስፋት በ113 ሚሊየን ብር ወጪ የሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል።

በጋዝጊብላና ደሃና ወረዳዎች እየተገነቡ የሚገኙት የመስኖ ፕሮጀክቶት 102 ሄክታር መሬት በማልማት 345 አባወራ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

አሁን ላይ በደሃና ወረዳ የኢቤ ወንዝ የካናል ስራ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት መግባቱን ጠቁመው በጋዝጊብላ ወረዳ የሚላና ዚባ ወንዝ የካናል ስራ በቀጣይ ወር እንደሚጠናቀቅ አመላክተዋል።

ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ የዝናብ አጠር የአየር ጠባይን በመቋቋም የአርሶ አደሩን የግብርና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ስርዓተ ምግብን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ገልፀዋል።

በጋዝጊብላ ወረዳ የቀበሌ 03 ነዋሪ አርሶ አደር አገኘሁ ጌታሁን በሰጡት አስተያየት በቀበሌያቸው እየተገነባ ያለው የመስኖ ተቋም ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት ሲገባም በክረምት ዝናብ ብቻ የተመሰረተውን የግብርና ልማትን በማሻሻል በመስኖ በመሰማራት እስከ ሶስት ጊዜ ማምረት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ ቀደም ሲል በተገነቡ የመስኖ ተቋማት 4 ሺህ 885 ሄክታር መሬት እየለማ መሆኑን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026