የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት የቀጣናውን እድገት የሚያፋጥን ነው

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት የቀጣናውን እድገት የሚያፋጥን መሆኑን ምሁራን ገለጹ።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ "የሀይል ጥገኝነትና መጭው ጊዜ" በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፍ አውደ ጥናት ተካሂዷል።

በአውደ ጥናቱም የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ለቀጠናው ኢኮኖሚያዊ ትስስር የራሱ ድርሻ ማበርከት እንደሚያስችል ተጠቁሟል።


በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉት በኖርዌይ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ላይፍ ሳይንስ የታዳሽ ሃይል ተመራማሪ ሳም አድራማላ (ፕ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከንፋስና ከሌሎች ከአካባቢ ብክለት ነጻ የሆኑ የታዳሽ ሃይል ልማቶች የሚደነቁ ናቸው።

ይህም የአፍሪካ ሃገራት የታዳሽ ሃይልን በጋራ አልምተው ለመጠቀም ለሚያደርጉት ጥረት መሰረት እንደሚሆን ጠቁመዋል።

ለአብነትም ከውሃ ሃይል ኤሌክትሪክ በማመንጨት ለጎረቤት ሃገራት በሽያጭ ማቅረቧ የቀጠናውን ትስስር በማጠናከር እድገትን የሚያፋጥን መሆኑን ጠቅሰዋል።

የታዳሽ ሃይል ልማት የነዳጅ ጥገኝነትን በማስቀረት ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ሽመልስ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው።

ኢትዮጵያ ከታዳሽ ሃይል ኤሌክትሪክ ማመንጨትና ከሃገር ውስጥ ፍጆታ አልፋ ለጎረቤት ሃገራት እያቀረበች መሆኑ ቀጠናዊ ትስስርን በማጠናከር ተደማሪ አቅም ነው ብለዋል።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ ይስሃቅ ሰቦቃ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከውሀ፣ ከንፋስና ከጂኦ ተርማል ከፍተኛ ሃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ጠቅሰዋል።


በዘርፉ ያለውን ሀገራዊ አቅም በማሳደግ ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ የኤሌክትሪክ መስመር በማይደርስባቸው አካባቢዎች በፀሃይ ሃይልና በሌሎች አማራጮች ለአርሶ አደሩ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን አንስተው አውደ ጥናቱም የዚሁ ትብብር አካል ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለታዳሽ ሃይል ያላትን ምቹ ስነ ምህዳር በአግባቡ ለመጠቀም የተለያዩ የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሃብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) ናቸው።

በተለይ ማገዶ አጠቃቀምን ከማሻሻል ጀምሮ ባዮጋዝን ጨምሮ ታዳሽ ሃይል በማመንጨት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በአውደ ጥናቱ ከስድስት በላይ የታዳሽ ሃይል የጥናት ውጤቶች ቀርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን የሃገር ውስጥና የውጭ የዘርፉ ምሁራን ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026