የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት የቀጣናውን እድገት የሚያፋጥን ነው

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት የቀጣናውን እድገት የሚያፋጥን መሆኑን ምሁራን ገለጹ።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ "የሀይል ጥገኝነትና መጭው ጊዜ" በሚል መሪ ሀሳብ ዓለም አቀፍ አውደ ጥናት ተካሂዷል።

በአውደ ጥናቱም የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ለቀጠናው ኢኮኖሚያዊ ትስስር የራሱ ድርሻ ማበርከት እንደሚያስችል ተጠቁሟል።


በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉት በኖርዌይ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ላይፍ ሳይንስ የታዳሽ ሃይል ተመራማሪ ሳም አድራማላ (ፕ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከንፋስና ከሌሎች ከአካባቢ ብክለት ነጻ የሆኑ የታዳሽ ሃይል ልማቶች የሚደነቁ ናቸው።

ይህም የአፍሪካ ሃገራት የታዳሽ ሃይልን በጋራ አልምተው ለመጠቀም ለሚያደርጉት ጥረት መሰረት እንደሚሆን ጠቁመዋል።

ለአብነትም ከውሃ ሃይል ኤሌክትሪክ በማመንጨት ለጎረቤት ሃገራት በሽያጭ ማቅረቧ የቀጠናውን ትስስር በማጠናከር እድገትን የሚያፋጥን መሆኑን ጠቅሰዋል።

የታዳሽ ሃይል ልማት የነዳጅ ጥገኝነትን በማስቀረት ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ሽመልስ ንጋቱ (ዶ/ር) ናቸው።

ኢትዮጵያ ከታዳሽ ሃይል ኤሌክትሪክ ማመንጨትና ከሃገር ውስጥ ፍጆታ አልፋ ለጎረቤት ሃገራት እያቀረበች መሆኑ ቀጠናዊ ትስስርን በማጠናከር ተደማሪ አቅም ነው ብለዋል።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ ይስሃቅ ሰቦቃ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከውሀ፣ ከንፋስና ከጂኦ ተርማል ከፍተኛ ሃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት ጠቅሰዋል።


በዘርፉ ያለውን ሀገራዊ አቅም በማሳደግ ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ የኤሌክትሪክ መስመር በማይደርስባቸው አካባቢዎች በፀሃይ ሃይልና በሌሎች አማራጮች ለአርሶ አደሩ የሃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን አንስተው አውደ ጥናቱም የዚሁ ትብብር አካል ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለታዳሽ ሃይል ያላትን ምቹ ስነ ምህዳር በአግባቡ ለመጠቀም የተለያዩ የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሃብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) ናቸው።

በተለይ ማገዶ አጠቃቀምን ከማሻሻል ጀምሮ ባዮጋዝን ጨምሮ ታዳሽ ሃይል በማመንጨት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በአውደ ጥናቱ ከስድስት በላይ የታዳሽ ሃይል የጥናት ውጤቶች ቀርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን የሃገር ውስጥና የውጭ የዘርፉ ምሁራን ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026