የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ሀዋሳ ከተማን ተወዳዳሪና ተመራጭ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው 

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሰር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የታሰበው የሀይቅ ዳርቻ ልማት ዲዛይን ይፋ ተደርጓል ።


ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማዋን ለኑሮ፣ ለስራ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው።

የልማት ስራዎቹ ከተማዋ ሀገር አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ስፖርታዊ ውድድሮችና ሌሎች ኹነቶችን በማስተናገድ ተመራጭ እንድትሆን አድርገዋታል ብለዋል።

የሀዋሳ ከተማን ለኑሮ ምቹና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም ህዝቡንና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ አቶ ደስታ ገልጸዋል።

በተለይም የኮሪደር ልማት ሀዋሳ የተቸረችውን የተፈጥሮ ውበት አጉልቶ ማውጣት መቻሉን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል።

ዛሬ ይፋ የተደረገው የሀይቅ ዳርቻ ልማት ተጨማሪ ውበትና የተወዳዳሪነት አቅም ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለተግባራዊነቱ በትብብር እንደሚሰራ አመላክተዋል።


የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል።

ህዝብን በማስተባበር የተሰራውና የሥራ ባህልን የቀየረው የኮሪደር ልማት የዚሁ አካል መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ከተማዋ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል መሆን መቻሏን ጠቁመዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በየነ በራሳን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለሀብቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026