🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ ገለጹ።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከመጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሥራ አፈፃጸም አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ፤ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት ብለዋል።
ለዚህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ ዕድገትን በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ፈጣንና ጤናማ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ በኢንቨስትመንት መሳተፍ አስደሳች መሆኑን ጠቁመው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካች አዎንታዊ ውጤቶች ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ምቹ የልማት ምኅዳር መፍጠሩን ተናግረዋል።
በቴሌኮም ዘርፍም አበረታች የቁጥጥር ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞች ቁጥር 13 ነጥብ 6 ሚሊየን ማድረስ ማስቻሉን አስረድተዋል።
ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ54 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን በመግለጽ።
የኤም-ፔሳ (M-PESA) ተጠቃሚዎች ቁጥር 5 ነጥብ 2 ሚሊየን መድረሱንና በመተግበሪያው የተደረገው የገንዘብ ዝውውርም 32 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መድረሱን አብራርተዋል።
የሞባይል ዳታ አገልግሎት በዓመታዊ ገቢ ላይ ትልቁን ድርሻ በመያዝ ጠንካራ ዕድገት ማሳየቱንም ጨምረው ጠቁመዋል።
በተጠናቀቀው የ2026 በጀት ዓመት 15 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንና ይህም የ130 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት እንዳለው አመላክተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026