የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ ገለጹ።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከመጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሥራ አፈፃጸም አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ፤ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት ብለዋል።

ለዚህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ ዕድገትን በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፈጣንና ጤናማ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ በኢንቨስትመንት መሳተፍ አስደሳች መሆኑን ጠቁመው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካች አዎንታዊ ውጤቶች ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ምቹ የልማት ምኅዳር መፍጠሩን ተናግረዋል።

በቴሌኮም ዘርፍም አበረታች የቁጥጥር ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞች ቁጥር 13 ነጥብ 6 ሚሊየን ማድረስ ማስቻሉን አስረድተዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ54 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን በመግለጽ።

የኤም-ፔሳ (M-PESA) ተጠቃሚዎች ቁጥር 5 ነጥብ 2 ሚሊየን መድረሱንና በመተግበሪያው የተደረገው የገንዘብ ዝውውርም 32 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መድረሱን አብራርተዋል።

የሞባይል ዳታ አገልግሎት በዓመታዊ ገቢ ላይ ትልቁን ድርሻ በመያዝ ጠንካራ ዕድገት ማሳየቱንም ጨምረው ጠቁመዋል።

በተጠናቀቀው የ2026 በጀት ዓመት 15 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንና ይህም የ130 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት እንዳለው አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026