🔇Unmute
ሀዋሳ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ማሳ በመስክ ተመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው።
በዚህም በበልግ ወቅት ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል።
በክልሉ ያለውን የእርሻ አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በበልግ ወቅት በክልሉ በሰብል የሚለማ የመሬት መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ አብዛኛው መሬት በምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ ከ152 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በስራስርና አትክልቶች መሸፈኑን ተናግረዋል።
አጠቃላይ ከለማው መሬትም ከ24 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።

በልማቱ እየተሳተፉ ካሉ መካከል በሎካ አባያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጽጌ ኩማ እንደገለጹት የአካባቢው 80 አርሶ አደሮች ከ75 ሄክታር በላይ ኩታ ገጠም መሬት ላይ በቆሎ እያለሙ መሆናቸውንና የማሳ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ሌላው በዳራራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ብንኦ 40 ሆነው በኩታገጠም በቆሎ እያለሙ መሆናቸውን ጠቁመው ምርቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በጋራ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026