የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።


ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ማሳ በመስክ ተመልክተዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው።


በዚህም በበልግ ወቅት ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል።


በክልሉ ያለውን የእርሻ አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


በበልግ ወቅት በክልሉ በሰብል የሚለማ የመሬት መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ አብዛኛው መሬት በምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።


የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ ከ152 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በስራስርና አትክልቶች መሸፈኑን ተናግረዋል።


አጠቃላይ ከለማው መሬትም ከ24 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።


በልማቱ እየተሳተፉ ካሉ መካከል በሎካ አባያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጽጌ ኩማ እንደገለጹት የአካባቢው 80 አርሶ አደሮች ከ75 ሄክታር በላይ ኩታ ገጠም መሬት ላይ በቆሎ እያለሙ መሆናቸውንና የማሳ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ሌላው በዳራራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ብንኦ 40 ሆነው በኩታገጠም በቆሎ እያለሙ መሆናቸውን ጠቁመው ምርቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በጋራ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026