🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የአፈር ለምነት ማሻሻያ ባለሙያ አምሳሉ አድማስ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግማሽ ያህሉን በ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ በመበተን ከአፈር ጋር የማዋሃድ ሥራ መሰራቱንና በቀሪው ማዳበሪያም ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ሳይንሳዊ አሰራሩን ተከትሎ በጥራት ከተዘጋጀ የአፈር ስነ ህይወታዊ ዘዴን በማሻሻል ለምነቱን በቀላሉ ለመመለስና ምርታማነትን ለማሳደገ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንምአስረድተዋል።
ባለፈው ዓመት በክልሉ ከ71 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት በማዘጋጀት ጥቅም ላይ መዋሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026