🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የአፈር ለምነት ማሻሻያ ባለሙያ አምሳሉ አድማስ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግማሽ ያህሉን በ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ በመበተን ከአፈር ጋር የማዋሃድ ሥራ መሰራቱንና በቀሪው ማዳበሪያም ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ሳይንሳዊ አሰራሩን ተከትሎ በጥራት ከተዘጋጀ የአፈር ስነ ህይወታዊ ዘዴን በማሻሻል ለምነቱን በቀላሉ ለመመለስና ምርታማነትን ለማሳደገ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንምአስረድተዋል።
ባለፈው ዓመት በክልሉ ከ71 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት በማዘጋጀት ጥቅም ላይ መዋሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026