🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እየተከናወኑ የሚገኙት የተቀናጁ የከተማ ልማት ስራዎች የከተማዋን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ከመጨመር ባለፈ የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ መሆናቸውን የከተማ ንድፍ እና የኪነ-ህንጻ ምሁራን ገለጹ።
ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ (NBC Ethiopia) “አዲሲቱ አዲስ” በሚል ርዕስ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

“የአዲስ አበባ ዘመናዊ ጉዞ ታሪካዊ ዳራ እና ልምዶች” በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ህንጻ መምህር ዳዊት በንቲ፤ አዲስ አበባ በምስረታዋ ወቅት በታቀደ የከተማ ፕላን ያልተጀመረች መሆኗን አስታውሰዋል።
በተለያዩ ዘመናት ከተማዋን ለማዘመን ሙከራዎች ቢደረጉም፣ በሚፈለገው ደረጃ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት እንዳልተቻለ ጠቁመዋል።
ይሁን እንጂ ከ2010 ዓ.ም ወዲህ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም ሰፋፊና ዘርፈ-ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ፓርኮችና አረንጓዴ ስፍራዎች መገንባታቸው የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ እየቀየሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በተጨማሪም የከተማዋ መገለጫ የሆኑት የወንዝ ዳርቻ ልማቶች፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገዶች ለነዋሪዎች ምቹ ከባቢ መፍጠራቸውን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል “የከተማ ትራንስፎርሜሽን እሳቤዎች፣ ትግበራ እና አንድምታዎች በአዲስ አበባ” በሚል ርዕስ ጽሁፍ ያቀረቡት የከተማ እና ቀጣናዊ ፕላኒንግ ከፍተኛ ተመራማሪ ኢንጂነር እሸትአየሁ ክንፉ፤ የአዲስ አበባ እድገት በታሪካዊ የፖለቲካ ለውጦች ላይ የተንተራሰ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀደሙት ዓመታት የከተማዋ አሰፋፈር ለቴክኖሎጂ እና ለዘመናዊ አገልግሎት አመቺ እንዳልነበረ አስታውሰው፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን የከተማ ማደስ ስራው ፍትሃዊ፣ ተወዳዳሪ እና ለኑሮ ምቹ ከተማን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
እነዚህ ስራዎች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተቀባይነት ከፍ እያደረጉት እንደሚገኙም አመልክተዋል።
የኤንቢሲ (NBC) ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ዘካርያስ ብርሀኑ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ አዲስ አበባ አሁን ላይ ግዙፍና ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበች መሆኗን ገልጸዋል።
በመሆኑም በመድረኩ የከተማዋ የልማት እንቅስቃሴዎች ከዓለምአቀፍ ተሞክሮዎች ጋር በማነጻጸር እንደሚዳሰሱና በተለያዩ የጥናት ጽሁፎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026