የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በግብርናው ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች የቤተሰብ ብልፅግና ማረጋገጥ ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶች ተገኝተዋል

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል በግብርናው ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች የቤተሰብ ብልፅግና ማረጋገጥ ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን የሲዳማ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ ገለፁ።

በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።


እንዲሁም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሸን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ለማ መሰለ(ዶ/ር) እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና የግብርና ሙያተኞች ተገኝተዋል።

የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ በክልሉ ልዩ ፀጋዎችና ዕድሎችን በመለየት የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ተቀርፀው ወደ ትግበራ መገባቱን ገልጸዋል።

በዚህም በሰብል፤ በአትክልትና ፍራፍሬና በቅመማቅመም እንዲሁም በእንስሳት ሀብት ልማት የክልሉን አቅም እና የገበያ ዕድሎችን በመለየት በተከናወኑ ስራዎች የቤተሰብ ብልፅግና ማረጋገጥ ያስቻሉ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን ገልፀዋል።

በቀጣይም ስኬቶችን በማስቀጠል ተረጂነትን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት በየደረጃው የመግባባትና ማቀናጀት ስራዎች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሸን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ በበኩላቸው በክልሉ በአብዛኛው ዞኖች የሴፍትኔት ተጠቃሚ እንደነበሩ አንስተዋል።

በዚህም እንደ ሀገር የተያዙ ራስን የመቻል ግቦችን በመከተል በክልሉ ያሉ ፀጋና ዕድሎችን ለይቶ ምርታማነትን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራቱን ጠቅሰዋል።

በዚህም ተጨባጭ ለውጦች ተመዝግበዋል ብለዋል።

ለአብነትም ከጥቂት ዓመት በፊት እህል ሲሰፈርላቸው የነበሩ በርካታ አርሶ አደሮች አሁን ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት እያንቀሳቀሱ መሆኑን አንስተዋል።

ክልሉ ተረጂ የነበሩ የማህበረሰብ ክፍሎቹን ከሌማት ትሩፋት፣ ከአረንጓዴ አሻራና ከሌሎች ሀገራዊ ኢኒሼቲቨች ጋር በማስተሳሰር ምርታማ የሆኑ አርሶ አደሮች መፍጠር መቻሉን ነው የገለፁት።

በተመሳሳይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ለማ መሰለ(ዶ/ር) ከልመና ወደ ብልፅግና የመሻገርና ሀገራዊ ክብርን የማስጠበቅ ግብ በመሰነቅ ወደ ትግበራ መገባቱን አንስተዋል።

ለዚህ ደግም የክልሉን ልዩ ፀጋና አቅም በመለየት በተሰሩ ስራዎች ከክልል አልፈው ለሀገር የተረፉ የግብርና ምርቶች እየተመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በተረጂነት ሕይወት ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን ምርታማ የማድረግ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026