የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሕይወት መስዋዕትነት የተገኘ ሉዓላዊነትን በላባችን ምሉዕ ማድረግ ይገባናል-አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡- በሕይወት መስዋዕትነት የተገኘ ሉዓላዊነትን በላባችን ምሉዕ ማድረግ ይገባናል ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለፁ።

በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቴ አለነ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ እና የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።


እንዲሁም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር ፤ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሸን ኮሚሽነር ወገኔ ብዙነህ፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ለማ መሰለ(ዶ/ር) እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና የግብርና ሙያተኞች ተገኝተዋል።

በዚሁ ወቅት አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንዳሉት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር የሀገር ወሳኝ አጀንዳ ስለመሆኑ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ የመሬት፣ አየር ፀባይ፣ውሃ ፤ የሰው ሀብት እንዲሁም የነፃነትና የሉዓላዊነት ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም ላለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ስንዴ ሲሰፈርላት የቆየች ሀገር መሆኗን አንስተዋል።

ይህ ተቃርኖ መታረቅ አለበት ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በሕይወት መስዋዕትነት የተገኘ ሉዓላዊነትን በላባችን ምሉዕ ማድረግ ይገባናል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ካላት ሁሉን አቀፍ ፀጋ አኳያ የምትለምን ሳይሆን የምትሰጥ ሀገር መሆኗን ተናግረዋል።

ስንዴ የሚሰፈርለት ሀገር ነፃነት ማረጋገጥ አይችልም ያሉት አቶ ተስፋሁን፤ ያለንን ሀገራዊ ሀብት ማቀናጀትና አንገት አስደፊ የሆነውን ተረጂነት ታሪክ ማድረግ ይገባናል ነው ያሉት።

የተረጂነት ዋና ችግር የሆነው የአስተሳሰብ ችግር በመሆኑ ከአስተሳሰብ ለውጥ ጀምሮ ራስን የመቻል ጉዞ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በዚህም ጉዳዩን ከንቅናቄ ባሻገር መዋቅራዊና ሰው ተኮር አድርጎ መተግበር፣ የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ እንደየ ዐውዱና አካባቢው ሁኔታ ለይቶ መተግበርና ቀጣይነት ያለው ተግባቦት መፍጠር ላይ በትኩረት እንዲሰራ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ለዚህ ደግሞ የሕዝብ ለህዝብ ውይይትና የሚዲያ ይዘት ስራዎችንም በዚህ ረገድ በትኩረትና በኃላፊነት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026