የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የቡና ላኪነት ሚና ይበልጥ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥታለች

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የቡና ላኪነት ሚና ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችል ስትራቴጂ ተግባራዊ በማድረግ በትኩረት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት የአፍሪካ ቡና ጉባኤን ለማስተናገድ የሚያስችላትን ስምምነት ከኢንተር-አፍሪካ የቡና ድርጅት (Inter-African Coffee Organization) ጋር ተፈራርማለች።


ስምምነቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሀደራ አበራ እና የኢንተር-አፍሪካ የቡና ድርጅት ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ሰለሞን ሩቴጋ ፈርመውታል።

አምባሳደር ሀደራ በወቅቱ እንደገለጹት፤ አፍሪካ በቡና ምርት የታደለች አህጉር ብትሆንም ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ሳታገኝ ቆይታለች።

ቡና ለኢትዮጵያ የምጣኔ ሀብት ዕድገትን ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ሕይወታቸውን የሚመሩበት ዋና የግብርና ምርት መሆኑን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቡና ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርጓትን የተለያዩ ተግባራት በትኩረት እያከናወነች እንደሚገኝ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸው፤ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የቡና ላኪነት ሚና ለማሳደግ የሚያስችል ስትራቴጂን ተግባራዊ አድርጋ እየሠራች ነው ብለዋል።

በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ፣ አቅማቸውን መገንባትና የቡና ጥራትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ለአብነት አንስተዋል።


ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከኢንተር-አፍሪካ የቡና ድርጅት ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም 25 ቡና አምራች የአፍሪካ ሀገራት የሚሳተፉበትን ይህንን ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ ኢትዮጵያ ሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

የኢንተር-አፍሪካ የቡና ድርጅት ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ሰለሞን ሩቴጋ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ይህንን ትልቅ የአፍሪካ የቡና ጉባኤ ለማስተናገድ በመስማማቷ ድርጅታቸው የተሰማውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል።

ዋና ጸሐፊው አክለውም፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላት የቡና ተወዳዳሪነትና ያካበተችው ሰፊ ልምድ ጉባኤው ስኬታማ እንዲሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ለዝግጅቱ መሳካት ድርጅታቸው አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በአፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያን ጨምሮ 25 ቡና አምራች ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት በመገናኘት የቡና ምርትና ምርታማነትን በተመለከቱ አጀንዳዎችና በዘርፉ ላይ በሚስተዋሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ በመምከር የመፍትሔ አቅጣጫ ሲያስቀምጡ ቆይተዋል።


ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት በቡና ዘርፍ ላይ የሚመክር ስብሰባ የምታስተናግድ መሆኗ ሀገሪቱ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝና ልምዷን ለሌሎች ሀገራት እንድታካፍል ትልቅ በር ይከፍታል ነው ያሉት።

በተጨማሪም አፍሪካውያን ነጻ የንግድ ቀጣናን ተጠቅመው እርስ በእርስ ቡና መገበያየት የሚችሉበትን ምቹ መድረክ እንደሚፈጥርም አመልክተዋል።

ዝግጅቱ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ከማነቃቃት ባለፈ የኢትዮጵያን ልዩ ልዩ የቡና ዝርያዎችና ባህላዊ የቡና አፈላል ሥርዓት ለዓለም ይበልጥ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026