የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ገለጸ።

የድሬደዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አብዱልሰላም መሐመድ (ዶ/ር) የተጠናቀቀውን የ2018 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብና የአዲሱን በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ አስመልክተው ለኢዜአ ገለጻ አድርገዋል።

በመግለጫውም በአስተዳደሩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የገቢ ምንጮችን ማስፋት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የገቢ አሰባሰቡን ዲጂታል በማድረግና ቅንጅታዊ አሠራርን በመተግበር በበጀት ዓመቱ ከ7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አንስተዋል።

የተሰበሰበው ገቢ ከታክስና ከማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች መሆኑን ገልጸው፣ ይህም የዕቅዱን 78 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል።

ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ2 ቢሊዮን 284 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለው አስታውቀዋል።

የሚሰበሰበው ገቢ እየጨመረ በመምጣቱ የሕዝቡን የመሠረተ ልማት፣ የመንገድ፣ የጤና፣ የውኃና የገጠር መስኖ ጥያቄዎችን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለመመለስ አስችሏል ብለዋል።

ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠልም በዘንድሮው በጀት ዓመት ከ13 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።


ከከተማዋ ግብር ከፋዮች መካከል አቶ ዮሴፍ አለባቸው እንዳሉት፤ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የዘረጋው ዘመናዊ የግብር መሰብሰቢያ አሠራር ግብር ከፋዮች ኃላፊነታቸውን በወቅቱ እንዲወጡ አድርጓል።

ግብር ከፋይ ወጣት ጽዮን ተከተል በበኩሏ፤ ግብርን መክፈል ለከተማዋ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መሠረታዊ መሆኑን በመረዳት የዜግነት ግዴታዋን መወጣቷን አንስታለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 21, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 8, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 4, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026