የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ማዕከሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ተደራሽ እያደረገ ነው

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ግንቦት 11/2018(ኢዜአ)፡- የሲናና ግብርና ምርምር ማዕከል የአርሶ አደርና አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያግዙ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

ማዕከሉ በምርምር ያገኛቸውን 12 የተሻሻሉ ዝርያዎች የለቀቀ ሲሆን፣ ዝርያዎቹ በሽታን የመቋቋም አቅማቸው ቀደም ሲል ከነበሩት የተሻሉ ከመሆናቸው ባሻገር፣ ከ14 እስከ 33 በመቶ የምርት ብልጫ ያላቸው እንደሆነም ተመላክቷል።

የሲናና ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አሰፋ ለኢዜአ እንዳሉት፣ ማዕከሉ የአርሶ አደርና አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በምርምር እየደገፈ ነው።


በተለይም ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት በስንዴ፣ በገብስና በሌሎች ስምንት የትኩረት መስኮች ላይ ምርምሮችን በማካሄድ 116 የምርምር ውጤቶችን ለተጠቃሚው ማድረሱን አስታውሰዋል።

በዘንድሮው የበጀት ዓመትም ባለፉት ስድስት ዓመታት በምርምር ሥር የነበሩ 12 የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለተጠቃሚው መልቀቁን አመልክተዋል።

በምርምር የተለቀቁት ዝርያዎች 4 የቦሎቄ ዝርያዎች፣ 2 የማሾ፣ 2 የድንች ዝርያዎችን ጨምሮ ሌሎች የአተር፣ የማሾ፣ የቆሎ ገብስ፣ የምስርና የባቄላ ዝርያዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።

አዳዲስ የተለቀቁት እነዚሁ ዝርያዎች በሽታን በመቋቋም አቅማቸው በፊት ከነበሩት ዝርያዎች የተሻሉ ከመሆናቸው ባሻገር፣ ከ14 እስከ 33 በመቶ የምርት ብልጫ ያላቸው እንደሆነም አመልክተዋል።

ዝርያዎቹ በብሔራዊ የዝርያ አጽዳቂ ኮሚቴ ከተገመገሙ በኋላ፣ ከሚያዝያ ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዕውቅና አግኝተው ለሕብረተሰቡ የተለቀቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በማዕከሉ የሰብል ምርምር የሥራ ሂደት አስተባባሪና ተመራማሪ አቶ ታደለ ታደሰ በበኩላቸው፣ ከተለቀቁት ዝርያዎች መካከል የቦሎቄ ዝርያዎቹ በሄክታር በአማካይ ከ19 እስከ 26 ኩንታል፣ እንዲሁም የድንች ዝርያዎቹ ከ500 እስከ 531 ኩንታል ምርት እንደሚሰጡ መረጋገጡን ተናግረዋል።

ዝርያዎቹ የተሻለ ምርት ከመስጠታቸው ባሻገር፣ ከነባር ዝርያዎች ጋር ሲነጻጸር ከ14 እስከ 33 በመቶ ጭማሪ እንዳላቸውም አመልክተዋል።

ዝርያዎቹ የባሌ ዞን ቆላና ወይናደጋን ጨምሮ ሌሎች ተመሳሳይ ሥነ-ምህዳር ባላቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ተስማሚ መሆናቸውንም ተመራማሪው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026