🔇Unmute
ሰመራ ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የመጠጥና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ።
ፕሮጀክቶቹን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ናቸው።
የተመረቁት ፕሮጀክቶች ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ይገጥማቸው የነበረውን የመጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት የሚፈቱ መሆኑ ተመላክቷል።

በተለይም አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች በመሄድ ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት የሚያስቀር መሆኑም ታውቋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖ እና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026