🔇Unmute
ሰመራ ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የመጠጥና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ።
ፕሮጀክቶቹን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ናቸው።
የተመረቁት ፕሮጀክቶች ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ይገጥማቸው የነበረውን የመጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት የሚፈቱ መሆኑ ተመላክቷል።

በተለይም አርብቶ አደሮች ውሃ ለማግኘት ሩቅ አካባቢዎች በመሄድ ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት የሚያስቀር መሆኑም ታውቋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱም የክልሉ አርብቶና አርሶ አደሮች በአካባቢው ያለውን ሰፊ መሬት በማልማት ምርታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖ እና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 7, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 3, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026