የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአፋር ክልል የተገነቡ የጠጠር መንገዶችና የብረት ድልድይ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች መካከል ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና የማህበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ታስበው የተገነቡ የጠጠር መንገዶችና የብረት ድልድይ ፕሮጀክቶች ተመርቀው በይፋ ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ።

ፕሮጀክቶቹን መርቀው ወደ ስራ ያስገቡት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባና የመስኖና ቆላማ አካቢዎች ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) ናቸው።


በዛሬው ዕለት ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የብረት ድልድዩን በውስጡ የያዘው የገቢ እና የኸሪ ራሱ ዞኖችን በዘላቂነት የሚያስተሳስረው የ64 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ፕሮጀክት አንዱ ነው።

ይህ የተመረቀው የመንገድ መሠረተ-ልማት በሁለቱ ዞኖች መካከል ያለውን ትስስር ከማጠናከሩ ባለፈ፣በመካከላቸው የሚገኙትን የገለአሉ እና የሰሙሮቢ ወረዳዎችን በቅርበት የሚያገናኝና የማህበረሰቡን የትራንስፖርት ችግር በከፍተኛ ደረጃ የሚያቃልል መሆኑ ተመላክቷል።

የጠጠር መንገዱና የብረት ድልድዩ 361 ሚሊዮን ብር የወጣበት ሲሆን ከ81 ሺህ በላይ ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑም ተመላክቷል።


የሀደለኤላ እና ሰሙሮቢ ወረዳዎችን የሚያስተሳስረውና ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ከወረዳና ከዞን ማዕከላት ጋር የሚያገናኘው የ18 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ፕሮጀክትም ሌላኛው ነው።

አዲስ ለተመረቀው የ18 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ፕሮጀክት 72 ሚሊዮን ብር በጀት የወጣ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ለልማት ሥራዎቹ 433 ሚሊዮን ብር በመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አማካኝነት ወጪ መደረጉ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026