የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከተረጂነት ወጥተን በጀመርነው የገቢ ማስገኛ ሥራ ተጠቃሚ ሆነናል-አርሶ አደሮች

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ከምግብ ዋስትና ፕሮግራም ተረጂነት ወጥተው በጀመሩት የገቢ ማስገኛ ሥራ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ለሌሎችም እንደተረፉ አርሶ አደሮች ገለጹ።

ግብርና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሃዋሳ ባዘጋጀው መድረክ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አርሶ አደሮች እንዳሉት፤ በገቢ ማስገኛ ሥራ ላይ መሰማራታቸው ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።

ከዚህ ቀደም በምግብ ዋስትና መርሀግብር ታቅፈው በሚያገኙት አነስተኛ ገቢ ህይወታቸውን ይመሩ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በመሰማራት ውጤታማ ከመሆን ባለፈ ለሌሎች መትረፍ እንደቻሉ ተናግረዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ሙዲ ሀሰን እንዳሉት፤ ለዓመታት በፕሮግራሙ ታቅፈው በሚያገኙት አነስተኛ ገቢ ሕይወታቸውን ሲመሩ ቆይተዋል።

በአካባቢያችን 65 ነዋሪዎች በመርሀግብሩ ድጋፍ ሲደረግልን ቆይተናል ያሉት አርሶ አደሩ፣ ከእነዚህ ውስጥ15ቱ በማህበር ተደራጅተው በንብ ማነብ እና በቅመማ ቅመም ልማት ሥራ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።

የንብ ማነብ ሥራውን በ25 ዘመናዊና ባህላዊ ቀፎ ታግዘው እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጸው፣ በአንድ ተኩል ሄክታር ማሳ ላይም ሮዝመሪ በማልማት 300 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በስልጤ ዞን ሁልባረግ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ካይሻ ኤርጌቾ፤ አካል ጉዳተኛ በመሆናቸው ለዓመታት በፕሮግራሙ በተደረገላቸው ድጋፍ ህይወታቸውን ሲመሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ያገኙትን ገንዘብ በመቆጠብ በጀመሩት የሱቅ እና አነስተኛ ግብርና ሥራ ገቢያቸውን በማሳደግ ከእርዳታ ሙሉ በሙሉ መውጣታቸውን ተናግረዋል።

በሀላባ ዞን የሲምቢጣ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገረመው መሀመድ፤ በቀበሌያቸው በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ምክንያት ለዓመታት ከቀዬያቸው በመፈናቀል ለተረጂነት ተዳርገው እንደነበር አስታውሰዋል።

በተደረገላቸው ድጋፍ ታግዘው በተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ መሰማራታቸውን ገልጸው፣ በዚህም ከተረጂነት ወጥተው በተለያየ አካባቢ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ሀብት ማፍራታቸውን ጠቅሰዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ነዋሪው ወጣት አርሶ አደር ታሪኩ ታደሰ በበኩሉ እንዳለው፣ ቀደም ሲል ምንም አይነት ገቢ ስላልነበረው በምግብ ዋስትና ፕሮግራም ሰርቶ በሚያገኘው አነስተኛ ገቢ ይተዳደር ነበር።

በአሁኑ ወቅት በቡና እና በሥራ ሥር ተክሎች ልማት ተሰማርቶ ገቢውን በማሳደግ 2 ሚሊዮን ብር ሀብት ማፍራቱን ተናግሯል።

በእዚህም ከእርዳታ ተላቆ ከራሱ ባለፈ በአቅራቢያው አቅመ ደካማ ቤተሰብ እያገዘ መሆኑንም ገልጿል።

ከሲዳማ ዞን ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ቀበሌ የነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ዴቢቴ ናሮ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በመርሀግብሩ ያገኙትን ገንዘብ በመቆጠብ በጀመሩት የዶሮና ፍየል እርባታ ሥራ ከእርዳታ ተላቅቀዋል።

በአሁኑ ወቅትም ያረቧቸውን ፍየሎች ለሌሎች በመስጠት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026