🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ የአካባቢውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና ቱሪዝም ልማት በማፋጠን የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች ገለጹ።
የከተማ አስዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኀላፊ አቶ ተመስገን ተድላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአውሮፕላን ማረፊያው የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ለማፋጠን የላቀ ድርሻ አለው።

በተለይ ባለሃብቶች ያጋጥማቸው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ ፕሮጀክቶቻቸውን በቅርበት ለመከታተልና ፣ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
በአካባቢው የሚመረቱ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በፍጥነት ወደ ገበያ ከማቅረብ በተጨማሪም የአውሮፕላን ማረፊያው አዳዲስ ባለሃብቶችን ለመሳብም መልካም እድል ይዞ መምጣቱን አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አእምሮ በበኩላቸው፤ የአውሮፕላን ማረፊያው የቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።

በዋናነትም የአባይ በረሃን አቋርጦ በመምጣት በአካባቢው የሚገኙ ቅርሶችን ለመጎብኘት ያጋጥም የነበረውን ችግር በመቅረፍ የጎብኝዎችን ቁጥር ለመጨመር የሚያስችል ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም የጮቄ ተራራን፣ ጥንታዊ ገዳማትና ሌሎች ቅርሶችን ለጎብኝዎች ክፍት ለማድረግም አሰጎብኝዎችን ከማደራጀት ጀምሮ ምቹ መስተንግዶ ለማቅረብ በተለየ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ሙሉጌታ ይስማው በበኩላቸው፤ የአውሮፕላን ማረፊያው መገንባት የዘመናት የህዝብ ጥያቄን በመፍታት የንግድ እንቅስቃሴን ለማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

አካባቢው በግብርናው ዘርፍ ትርፍ አምራች ከመሆኑም በላይ ያለውን የማዕድን ሃብት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማእከል ለማድረግ መልካም እድል ይዞ መምጣቱን ጠቁመው ይህም በአገልግሎት ዘርፉ የተሰማሩ ግለሰቦች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል ።
በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በግንባታ ላይ ያሉ ኢንዱስትሪዎችን ፈጥኖ በማጠናቀቅ አካባቢውን የንግድ ማእከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026