🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጠናቀቅ የአካባቢውን የኢንቨስትመንት፣ የንግድና ቱሪዝም ልማት በማፋጠን የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች ገለጹ።
የከተማ አስዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኀላፊ አቶ ተመስገን ተድላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአውሮፕላን ማረፊያው የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ለማፋጠን የላቀ ድርሻ አለው።

በተለይ ባለሃብቶች ያጋጥማቸው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ ፕሮጀክቶቻቸውን በቅርበት ለመከታተልና ፣ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
በአካባቢው የሚመረቱ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በፍጥነት ወደ ገበያ ከማቅረብ በተጨማሪም የአውሮፕላን ማረፊያው አዳዲስ ባለሃብቶችን ለመሳብም መልካም እድል ይዞ መምጣቱን አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አእምሮ በበኩላቸው፤ የአውሮፕላን ማረፊያው የቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።

በዋናነትም የአባይ በረሃን አቋርጦ በመምጣት በአካባቢው የሚገኙ ቅርሶችን ለመጎብኘት ያጋጥም የነበረውን ችግር በመቅረፍ የጎብኝዎችን ቁጥር ለመጨመር የሚያስችል ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም የጮቄ ተራራን፣ ጥንታዊ ገዳማትና ሌሎች ቅርሶችን ለጎብኝዎች ክፍት ለማድረግም አሰጎብኝዎችን ከማደራጀት ጀምሮ ምቹ መስተንግዶ ለማቅረብ በተለየ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ ንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ሙሉጌታ ይስማው በበኩላቸው፤ የአውሮፕላን ማረፊያው መገንባት የዘመናት የህዝብ ጥያቄን በመፍታት የንግድ እንቅስቃሴን ለማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

አካባቢው በግብርናው ዘርፍ ትርፍ አምራች ከመሆኑም በላይ ያለውን የማዕድን ሃብት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማእከል ለማድረግ መልካም እድል ይዞ መምጣቱን ጠቁመው ይህም በአገልግሎት ዘርፉ የተሰማሩ ግለሰቦች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል ።
በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በግንባታ ላይ ያሉ ኢንዱስትሪዎችን ፈጥኖ በማጠናቀቅ አካባቢውን የንግድ ማእከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 7, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 3, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026