🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ከለውጡ በፊት ከ10ሺህ በታች የነበረው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችበለውጡ አመታት በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከ43ሺህ በላይ መድረሳቸውን የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሞጆ ከተማ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀዋል።
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የኦሮሚያ ክልልን የኢንቨስትመንት ማዕከል ለማድረግና የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሞተር እንዲሆን በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የመደመር እሳቤን መሠረት በማድረግ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ሰፊ ሥራ መሠራቱንም ገልጸዋል።
በክልሉ ቡልቡላ እና ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የነቀምቴ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግንባታው የተጀመረውን ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በዋቢነት አንስተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ብቻ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ባለሃብቶች ወደ ኢንቨስትመንት ለመግባት በሂደት ላይ እንደሚገኙ እና ከ30 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሰዋል ብለዋል።
የክልሉ መንግሥት ቢሮክራሲን በመቀነስ፣ አሠራሮችን በማሳለጥ፣ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት እና ወጣቶች ክህሎት ይዘው የልማቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን እየፈጠረ መሆኑንም አስታውቀዋል።
የዛሬው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ምረቃም የዚሁ እንቅስቃሴ ውጤት አካል መሆኑን ነው የገለጹት።
የግብርናው ዘርፍም ከተለመደው አሠራር ወጥቶ ወደ ኢንቨስትመንት እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው መንገድ በቁርጠኝነት ከተሠራ የክልሉም ሆነ የሀገሪቱ ብልጽግና በአጭር ጊዜ እውን እንደሚሆን ተናግረዋል።
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 7, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 3, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026