የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት የሚውሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች በስፋት ተዘጋጅተዋል

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ግንቦት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት የሚውሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ዘይቱን፣ ሎሚ፣ አፕል፣ ማንጎ፣ ግሽጣና ቴምር ይገኙበታል።

የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሐመድሳኒ አሚን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ ይገኛሉ።

የዚሁ አካል የሆነውን የሙዝ ልማት ይበልጥ ለማሳካትና ምርጥ የሙዝ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ፣ ባቱን ጨምሮ ከተለያዩ የክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


ለአብነትም ባለፉት ዓመታት ከ58 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሙዝ ልማት የተሸፈነ ሲሆን፤ ሥራውን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ60 ሚሊዮን በላይ የሙዝ ችግኞች በምርምር ማዕከላትና በአርሶ አደሩ ማሳዎች ላይ እንዲባዙ ተደርጎ ለተከላ ተዘጋጅተዋል ብለዋል።

የሙዝ ልማቱን ስኬታማ ለማድረግ ከክረምት ወቅት ባለፈ፤ በተለያዩ የክልሉ ዞኖች የበጋ መስኖ ልማት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ልማቱን በማስፋፋት ረገድ ከዚህ ቀደም የሙዝ ምርት በማይታወቅበት በምሥራቅ ሸዋ ዞንና በሌሎች የክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጭምር በስፋት እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።

የሙዝ ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ፤ አማራጭ የገቢ ምንጭን ለማስፋትና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ለፓፓያ ልማትም 100 ሚሊዮን የሚጠጉ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን፤ እነዚህን ችግኞች ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር የማስተሳሰር ሥራ ተጀምሯል ነው ያሉት።

በተጨማሪም በክልሉ የፍራፍሬ ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋት የአቮካዶ፣ የብርቱካን፣ የዘይቱን፣ የሎሚ፣ የአፕል፣ የማንጎ፣ የግሽጣና የቴምር ችግኞችን በጥራት የማዘጋጀት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026