🔇Unmute
አዳማ፤ ግንቦት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለምግብነት የሚውሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
ከተዘጋጁት ችግኞች መካከል ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ ዘይቱን፣ ሎሚ፣ አፕል፣ ማንጎ፣ ግሽጣና ቴምር ይገኙበታል።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሐመድሳኒ አሚን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ ይገኛሉ።
የዚሁ አካል የሆነውን የሙዝ ልማት ይበልጥ ለማሳካትና ምርጥ የሙዝ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ፣ ባቱን ጨምሮ ከተለያዩ የክልሉ የግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ለአብነትም ባለፉት ዓመታት ከ58 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሙዝ ልማት የተሸፈነ ሲሆን፤ ሥራውን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ60 ሚሊዮን በላይ የሙዝ ችግኞች በምርምር ማዕከላትና በአርሶ አደሩ ማሳዎች ላይ እንዲባዙ ተደርጎ ለተከላ ተዘጋጅተዋል ብለዋል።
የሙዝ ልማቱን ስኬታማ ለማድረግ ከክረምት ወቅት ባለፈ፤ በተለያዩ የክልሉ ዞኖች የበጋ መስኖ ልማት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ልማቱን በማስፋፋት ረገድ ከዚህ ቀደም የሙዝ ምርት በማይታወቅበት በምሥራቅ ሸዋ ዞንና በሌሎች የክልሉ ቆላማ አካባቢዎች ጭምር በስፋት እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።
የሙዝ ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ፤ አማራጭ የገቢ ምንጭን ለማስፋትና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።
ለፓፓያ ልማትም 100 ሚሊዮን የሚጠጉ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን፤ እነዚህን ችግኞች ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር የማስተሳሰር ሥራ ተጀምሯል ነው ያሉት።
በተጨማሪም በክልሉ የፍራፍሬ ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋት የአቮካዶ፣ የብርቱካን፣ የዘይቱን፣ የሎሚ፣ የአፕል፣ የማንጎ፣ የግሽጣና የቴምር ችግኞችን በጥራት የማዘጋጀት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስታውቀዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026