የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በክረምቱ ወራት ከ3 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሻይ ችግኝ ይለማል

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ክረምት ከ3 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሻይ ችግኝ በኩታገጠም እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ቻላቸው አዱኛ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በክልሉ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ለሻይ ልማት ዘርፍ ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።


ክልሉ ምቹ የአየር ንብረት፣ በቂ የዝናብ መጠንና ለሻይ ተክል ተስማሚ የአፈር ዓይነት ያለው በመሆኑ ለዘርፉ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ጠቁመዋል።

ይህንን ተከትሎም ልማቱ በስፋት እየተከናወነ የሚገኘው የዞኖቹን መልክዓ ምድርና የአየር ንብረት መሰረት በማድረግ ሲሆን፤ በተለይም በጅማ፣ ኢሉአባቦር እና ቡኖ በደሌ ዞኖች ውስጥ በስፋት እየለማ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ በዘንድሮው ዓመት ከተዘጋጀው 120 ሚሊዮን የሻይ ችግኝ ውስጥ፤ 42 ሚሊዮኑን በ3 ሺህ 168 ሄክታር መሬት ላይ በኩታገጠም ለመትከል ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ነው ያሉት።

ለዚህም እንዲረዳ የመሬት ልየታ ተካሂዶ በክላስተር የተደራጀ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የጉድጓድ ቁፋሮ እና የሻይ ችግኝ ተከላ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

ከዘርፉ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግም የተሻሻሉ ዝርያዎች የሚባዙባቸው የሻይ ችግኝ ጣቢያዎች በመንግስትና በአርሶ አደሮች ደረጃ ለተከላ ተዘጋጅተዋል ብለዋል።

በዘንድሮው የልማት ስራ 1 ሺህ 250 አርሶ አደሮች የሚሳተፉ ሲሆን፤ የሻይ ተክል ችግኞችን በኩታገጠም አሰራር ዘዴ ለመትከል ሙሉ ዝግጅት አድርገዋል ሲሉም አረጋግጠዋል።

እስካሁን ባለው ሂደት በክልሉ በአጠቃላይ 2 ሺህ 700 ሄክታር መሬት በሻይ ተክል መሸፈኑን ጠቁመው፤ ከ1 ሺህ 200 በላይ አርሶ አደሮችም እየተሳተፉበት ይገኛል ነው ያሉት።

አርሶ አደሩ ለሚያመርተው የሻይ ምርት አስተማማኝ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ በስፋት እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቅሷል።

በክልሉ ምዕራብ አካባቢዎች ባለው ከፍተኛ የዝናብ መጠን ምክንያት የመሬት አሲዳማነት ይከሰታል።

የሻይ ተክል ደግሞ ይህንን የአፈር አሲዳማነት ተቋቁሞ ከፍተኛ ምርት መስጠት የሚችል በመሆኑ፣ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅና የአርሶ አደሩን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራበት ሲሉም ተናግረዋል።

ይህ የሻይ ልማት አሲዳማ መሬትን የመቋቋም አቅም ያለው በመሆኑ፤ በአሁኑ ወቅት መሰል የአፈር ችግር ባለባቸው በሌሎች የክልሉ አካባቢዎችም ልማቱን ለማስፋፋት ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን አቶ ቻላቸው አዱኛ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026