የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቦረና ሕዝብ ከተረጅነት ነፃ መውጣቱ በተግባር የታየ ትልቅ ለውጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ግንቦት 19 /2018 (ኢዜአ)፦የቦረና ሕዝብ ያሳየው የታታሪነትና የሥራ ወዳድነት መንፈስ የተፈጥሮ ጸጋን ተጠቅሞ ከረሃብ መውጣት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያመለከቱት በምስራቅ ቦረና ዞን ሊበን ወረዳ በሜካናይዜሽን የታገዘውንና በክላስተር እየለማ የሚገኘውን ሰፊ የስንዴ ማሳ በጎበኙበት ወቅት ነው።


የአካባቢው ማህበረሰብ ከጥቂት ዓመታት በፊት ይደርስበት ከነበረው ተደጋጋሚ የድርቅ አደጋና የውኃ እጥረት ፈተና ተላቆ፣ በአሁኑ ወቅት በአረንጓዴ ልማት አዲስ ምዕራፍ እየጻፈ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

ቀደም ሲል እስከ 90 በመቶ የሚደርሰው የዞኑ ነዋሪ በሴፍቲኔት ድጋፍ ይተዳደር እንደነበርና ማህበራዊ ሁነቶች እንኳ ሳይቀሩ በእርዳታ እህል ይከናወኑ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዛሬ ላይ ግን ያ የድህነት ታሪክ ተቀይሮ የተረጅነት ምጣኔው ወደ ዜሮ መውረዱን ይፋ አድርገዋል።

ይህ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመዘገበውና ማህበረሰቡን ከእርዳታ ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ያላቀቀው ስኬት በቃላት ሊገለጽ የማይችል ተዓምር መሆኑን ገልጸዋል።

በዘንድሮው አውድማ በሊበን ወረዳ ብቻ 250 ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል መሸፈኑን ጠቁመው፤ የተሻሻሉ የውኃ አማራጮችን በመጠቀም ምርታማነቱን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚቻልና ይህም ከአገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርትን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ዕድል እንደሚፈጥር አመላክተዋል።

ቀደም ሲል የረድኤት እህል ይከፋፈልበት የነበረው ስፍራ ዛሬ ወደ ሰፊ የምርት ማዕከልነት ተለውጦ ማየት ታላቅ ደስታን የሚፈጥር መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ አይነቱ አመርቂ የልማት ተሞክሮ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም ሊሰፋ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በርትቶ በመስራት ከልመናና ከረሃብ መውጣት እንደሚቻል የቦረና ሕዝብ በተግባር ማሳየቱንም አክለዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማጠቃለያቸው፤ የቦረና ሕዝብ ያሳየው ታታሪነት እና የስራ ወዳድነት መንፈስ የተፈጥሮ ጸጋንና እውቀትን አቀናጅቶ በመጠቀም ረሃብንና ጥገኝነትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ የሰጠ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026