የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአዳማ ከተማ በተለያዩ ዘርፎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ነዋሪዎች ውጤታማ በመሆናቸው ለሌሎች ወጣቶችም የሥራ ዕድል ፈጥረዋል

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ በአዳማ ከተማ በተለያዩ ዘርፎች የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ነዋሪዎች ውጤታማ በመሆናቸው ለሌሎች ወጣቶችም የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ገለጹ።


ከተጠቃሚዎቹ መካከል አቶ ጌቱ ተስፋዬ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ከተማ አስተዳደሩ በቤተሰብ ብልጽግና ተደራጅተው ራሳቸውንና ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ከፍተኛ ድጋፍ እንዳደረገላቸው ገልጸዋል።

በከተማዋ ቦሌ ክፍለ ከተማ በተመቻቸላቸው የመሥሪያ ቦታ ላይ ከአምስት የቤተሰብ አባላት ጋር በመደራጀት በዚህ ዓመት ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።


መንግሥት ባመቻቸላቸው የ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ብድር በዳቦ ማምረቻ ኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ምርታቸውን ለአካባቢው ማኅበረሰብ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን አስረድተዋል።

አሁን ላይ ከራሳቸው አልፈው ለ10 ተጨማሪ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን አውስተዋል።


ሌላኛው በዱቄት ማምረቻ ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ገዙ በዳዳ በበኩላቸው፤ መንግሥት ወደ ልማት እንዲገቡ እንዲሁም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።

ከተማ አስተዳደሩ የመሥሪያ ቦታ ከመስጠትና መሠረተ ልማት ከማሟላት ባለፈ፣ ከባንክ የ2 ሚሊዮን ብር ብድር እና የካፒታል ማሽን አቅርቦት እንዲያገኙ በማመቻቸት በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ድጋፍ ማድረጉን አመልክተዋል።


አቶ ገዙና የቤተሰባቸው አባላት የዱቄት ማምረቻ ማኅበር በቀን 330 ኩንታል የስንዴ ዱቄት በማምረት ለዳቦ ፋብሪካዎችና ለኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ ይገኛሉ ብለዋል።

በዚህም ውጤታማ መሆን ከመቻላቸው ባለፈ ለስምንት ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።


የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የቤተሰብ ብልጽግና ፓኬጅ በከተማዋ በተደራጀ መልኩ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ይህ አሠራር እያንዳንዱን ቤተሰብ ለለውጥና ለዕድገት በማነቃቃት፣ ለመበልፀግ በቁጭት እንዲነሱ ማድረጉን ጠቁመው፤ ተሳታፊዎች የጠራ ግንዛቤ ይዘው ሥራ ውስጥ እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

በበጀት ዓመቱ ለቤተሰብ ብልጽግና ተሳታፊዎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባው፤ ለዚህም አስተዳደሩ የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎችን እንዲሁም የብድር አቅርቦትን ለማመቻቸት እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህ ዓመት በከተማዋ በተገነቡ በርካታ ሼዶች 89ሺህ የከተማዋ ወጣቶችና ነዋሪዎች በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ዘርፎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026