🔇Unmute
ባህርዳር ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዘንድሮው መኸር እርሻ ከ876ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ለኢንዱስትሪና ለውጭ ገበያ የሚውል የሰሊጥና የአኩሪ አተር እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
ሰሊጥ ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከሚያስገኙ የግብርና ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ነው።
አኩሪ አተርም ለምግብ ዘይት ፋብሪካዎችና ለእንስሳት መኖ ኢንዱስትሪዎች ወሳኝ ግብዓት ከመሆኑም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ተፈላጊነት እየጨመረ የመጣ ሰብል ነው።
በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት ለኢንዱስትሪና ለወጪ ምርት ግብዓት የሚውሉ ሰብሎችን በጥራትና በብዛት ለማምረት ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው።

በዚህም በዘንድሮው የመኸር እርሻ የአየር ንበረታቸውና ስነ ምህዳራቸው ተስማሚ በሆኑ አካባቢዎች የሰሊጥና አኩሪ አተር ሰብሎች በስፋት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል።
በዚህም በክልሉ ከሚለማው 876ሺህ 870 ሄክታር መሬት፤ 463ሺህ 566 ሄክታር በሰሊጥ ቀሪው ደግሞ በአኩሪ አተር እንደሚለማ ተናግረዋል።
ከልማቱ ከ15 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው የዘር ወቅት በመድረሱም ዘርና ማዳበሪያ እየቀረበ ነው ብለዋል።
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026