🔇Unmute
አዳማ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የህዝብ ተሳትፎ የልማት መነሳሳትን እንደሚያጠናክር የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
አስተያየት ሰጪዎቹ እንደተናገሩት፤ በምርጫው የታየው ተሳትፎ ለልማት እና ለእድገት በጎ አስተዋጽኦ ያለው ነው።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ሲስተር ዓለም ጀማል እንዳሉት፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየው የህዝብ ተሳትፎ በትብብር እና በህብረት ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ማሻገር እንደሚቻል ያሳየ ነው።
በአዳማ ከተማ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።
ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ንጉሴ ኦብሴ፤ ህዝቡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሌሊት ብርድና በረጃጅም ሰልፎች ሳይበገር ያሳየው ጽናትና ቁርጠኝነት፣ ለልማት ያለውን መነሳሳት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ የሚጠበቅብኝን እወጣለሁ ብለዋል።
አቶ ጌታቸው ወርቅነህ በበኩላቸው በምርጫው የታየው የህዝብ ተሳትፎ ህዝቡ ለሰላምና ለልማት ያለውን ተነሳሽነት በግልጽ ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
ወደ ፊትም አንድነታችንን በማጠናከር በልማት ስራዎች ላይ መረባረብ አለብን ብለዋል።
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026