የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በጠቅላላ ምርጫው የታየው የህዝብ ተሳትፎ የልማት መነሳሳትን የሚያጠናክር ነው -የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች

Jun 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የህዝብ ተሳትፎ የልማት መነሳሳትን እንደሚያጠናክር የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

አስተያየት ሰጪዎቹ እንደተናገሩት፤ በምርጫው የታየው ተሳትፎ ለልማት እና ለእድገት በጎ አስተዋጽኦ ያለው ነው።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ሲስተር ዓለም ጀማል እንዳሉት፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየው የህዝብ ተሳትፎ በትብብር እና በህብረት ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ማሻገር እንደሚቻል ያሳየ ነው።

በአዳማ ከተማ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ ንጉሴ ኦብሴ፤ ህዝቡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሌሊት ብርድና በረጃጅም ሰልፎች ሳይበገር ያሳየው ጽናትና ቁርጠኝነት፣ ለልማት ያለውን መነሳሳት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እንዲቀጥሉ የሚጠበቅብኝን እወጣለሁ ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ወርቅነህ በበኩላቸው በምርጫው የታየው የህዝብ ተሳትፎ ህዝቡ ለሰላምና ለልማት ያለውን ተነሳሽነት በግልጽ ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

ወደ ፊትም አንድነታችንን በማጠናከር በልማት ስራዎች ላይ መረባረብ አለብን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026