የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግ ስራ እየተከናወነ ነው

Jun 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ግንቦት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የቡና አብቃይ ወረዳዎች የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የጋምቤላ ክልል ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለተለያዩ ሰብሎች ልማት ምቹ የአየር ንብረትና ሰፊ ለም መሬት ካላቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች አንዱ ቢሆንም፣ የቡና ልማት ዘርፉ ግን ካለው ከፍተኛ እምቅ አቅም አንጻር በተገቢው ሳይለማ ለረጅም ዓመታት ቆይቷል።

በተለይም እንደ ጋዶ፣ የጎደሬ ወረዳን ጨምሮ አንዳንድ የምዕራብ አኙዋክ አካባቢዎች ለቡና ልማት እጅግ ተስማሚ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር አለው።

በእነዚህ ወረዳዎች የተራቆቱ አካባቢዎችን ከአረንጓዴ አሻራ ልማት ጋር በማቀናጀት በቡናና ጥምር የጥላ ዛፍ በመሸፈን ስነ-ምህዳርን በማሻሻልና የዘርፉን ምርታማነት በመጨመር ረገድ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።


የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በማጃንግ ዞን በሚገኙ የመንጌሽና የጎደሬ ቡና አብቃይ ወረዳዎች የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ ነባር ዝርያዎችን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በመተካትና በተራቆቱ አካባቢዎች የቡና ጥምር ደን ልማትን በማስፋት ምርታማነትን የማሳደግ ስራ እንደሚከናወን ነው የገለጹት።

በዘንድሮው ክረምት ከአረንጓዴ አሻራ ልማቱ ጋር በማቀናጀት በፕሮጀክቶች፣ በባለሃብቶችና በአርሶ አደሮች ከ4 ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች መዘጋጀታቸውን አቶ አንድሮው ተናግረዋል።


በቢሮው የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ገዳሙ እንዳሉት የተሻሸሉ የቡና ዝርያዎችን ከቴፒና ከጅማ ግብርና ምርምር ተቋማት በማምጣት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ነው።

በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራሙ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተለይም በጎደሬ ወረዳ በሞዴል አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም የቡና ማሳና በሰርቶ ማሳያዎች የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን የማስፋትና የማስተዋወቅ ስራ ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።

በዘንድሮው ክረምትም ከ250 ሺህ የሚበልጡ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በኩታ ገጠም ለሚያለሙና ለሌሎች ሞዴል አርሶ አደሮች ለማሰራጨት ችግኞቹ መዘጋጀታቸውን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል።

በማጃንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች ካገኙ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ዝናቤ ቢለው በሰጡት አስተያየት በተራቆቱ አካባቢዎች የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ከጥምር የደን ዛፍ ጋር አቀናጅቶ በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በቀጣይም በተመሳሳይ መልኩ የቡና ጥምር ደን ልማቱን በማስፋትና ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የተራቆቱ አካባቢዎችን በቡናና በጥምር የጥላ ዛፍ በማልማት አካባቢውን ወደ ነበረበት በመመለስና ከዘርፉም ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው የዚሁ ቀበሌ አርሶ አደር አቶ ከድር ሙሀመድ ናቸው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026