🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ከማረጋገጥ አንጻር አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ (Visa) ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን አዲስ የግብይትና የክፍያ ካርድ አገልግሎት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ባንኩ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዚህም የባንኩ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባማይልስ (ShebaMiles) ደንበኞች በጋራ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ (CBE-ET Cobranded Visa Prepaid Card) ዛሬ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ የሼባማይልስ አባላት የኢ-ኮሜርስ ክፍያዎችን በቀላሉ መፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፥ በሚያደርጉት ግብይትም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ በር ይከፍታል ብለዋል።
ደንበኞች በካርዱ ግብይት በሚፈጽሙበት ወቅት የሼባማይልስ ነጥቦችን የሚያከማቹ ሲሆን፥ የተሰበሰቡትን ነጥቦች ለአውሮፕላን ትኬት መግዣና ለሌሎች የሼባማይልስ ማበረታቻ ጥቅማጥቅሞች ማዋል እንደሚችሉ አብራርተዋል።
የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው፤ የዚህ የቪዛ ካርድ ይፋ መሆን ለአየር መንገዱ የሼባማይልስ ደንበኞች ዘመናዊና የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026