የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባንኩ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማረጋገጥ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute


አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተደራሽ በማድረግ የደንበኞቹን ፍላጎት ከማረጋገጥ አንጻር አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ (Visa) ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን አዲስ የግብይትና የክፍያ ካርድ አገልግሎት ዛሬ ይፋ አድርጓል።


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ባንኩ በዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


በዚህም የባንኩ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባማይልስ (ShebaMiles) ደንበኞች በጋራ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ (CBE-ET Cobranded Visa Prepaid Card) ዛሬ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።


ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ የሼባማይልስ አባላት የኢ-ኮሜርስ ክፍያዎችን በቀላሉ መፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፥ በሚያደርጉት ግብይትም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ በር ይከፍታል ብለዋል።


ደንበኞች በካርዱ ግብይት በሚፈጽሙበት ወቅት የሼባማይልስ ነጥቦችን የሚያከማቹ ሲሆን፥ የተሰበሰቡትን ነጥቦች ለአውሮፕላን ትኬት መግዣና ለሌሎች የሼባማይልስ ማበረታቻ ጥቅማጥቅሞች ማዋል እንደሚችሉ አብራርተዋል።


የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው፤ የዚህ የቪዛ ካርድ ይፋ መሆን ለአየር መንገዱ የሼባማይልስ ደንበኞች ዘመናዊና የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026