የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ዓመት 370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ ይተከላል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ዓመት 370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ እንደሚተከል የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በጅማ ዞን ማና ወረዳም የዘንድሮው የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በይፋ ተጀምሯል።

በስፍራው ተገኝተው መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ፤ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።


ዘንድሮ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን የቡና ችግኞች ተዘጋጅተው በ370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየተተከሉ መሆኑን እና ይህም የክልሉን አጠቃላይ የቡና ምርት ሽፋን ወደ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ከፍ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

በቀጣይም ምርታማነቱን ይበልጥ ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በመተባበር የተሻሻሉ ዝርያዎችን የማቅረቡ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት 300 ሺህ ሄክታር ብቻ የነበረው የዞኑ የቡና ሽፋን አሁን ላይ ከ600 ሺህ ሄክታር በላይ መድረሱን ተናግረዋል።


በዘንድሮው ዓመትም 700 ሚሊዮን ችግኞችን ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለመትከል ታቅዶ ስራው ተጀምሯል ብለዋል።

የማና ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰመሩዲን አህመድ፤ በወረዳው 9 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ በተጀመረው ስራ፣ በዛሬው ዕለት ብቻ በህዝብ ተሳትፎ በ100 ሄክታር መሬት ላይ ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል።


የወረዳው አርሶ አደሮች በክላስተር ተደራጅተው በመስኖ ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ምርታማነታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም አክለዋል።

የማና ወረዳ ዶዩ ቢቂላ ቀበሌ አርሶ አደሮች የሆኑት ጋሊ አባዝናብ እና ሀፊዝ በድሩ በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም ቡናን በግላቸው ለማምረት ባደረጉት ጥረት ያገኙት የነበረው ምርት አነስተኛ እንደነበር አስታውሰዋል።


"አሁን ላይ ግን በክላስተር ተደራጅተን ማምረት በመጀመራችን ተጠቃሚ መሆን ችለናል፤ ምርትና ምርታማነታችንም እያደገ መጥቷል" ብለዋል።

አርሶ አደሮቹ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት አስፈላጊው ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው በመሆኑ በዘንድሮው የምርት ዘመን ከፍተኛ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026