የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ዓመት 370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ ይተከላል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ዓመት 370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ እንደሚተከል የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በጅማ ዞን ማና ወረዳም የዘንድሮው የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በይፋ ተጀምሯል።

በስፍራው ተገኝተው መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ፤ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።


ዘንድሮ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን የቡና ችግኞች ተዘጋጅተው በ370 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ እየተተከሉ መሆኑን እና ይህም የክልሉን አጠቃላይ የቡና ምርት ሽፋን ወደ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ከፍ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

በቀጣይም ምርታማነቱን ይበልጥ ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በመተባበር የተሻሻሉ ዝርያዎችን የማቅረቡ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት 300 ሺህ ሄክታር ብቻ የነበረው የዞኑ የቡና ሽፋን አሁን ላይ ከ600 ሺህ ሄክታር በላይ መድረሱን ተናግረዋል።


በዘንድሮው ዓመትም 700 ሚሊዮን ችግኞችን ከ200 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለመትከል ታቅዶ ስራው ተጀምሯል ብለዋል።

የማና ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰመሩዲን አህመድ፤ በወረዳው 9 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና ለመሸፈን ታቅዶ በተጀመረው ስራ፣ በዛሬው ዕለት ብቻ በህዝብ ተሳትፎ በ100 ሄክታር መሬት ላይ ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል።


የወረዳው አርሶ አደሮች በክላስተር ተደራጅተው በመስኖ ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ምርታማነታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም አክለዋል።

የማና ወረዳ ዶዩ ቢቂላ ቀበሌ አርሶ አደሮች የሆኑት ጋሊ አባዝናብ እና ሀፊዝ በድሩ በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም ቡናን በግላቸው ለማምረት ባደረጉት ጥረት ያገኙት የነበረው ምርት አነስተኛ እንደነበር አስታውሰዋል።


"አሁን ላይ ግን በክላስተር ተደራጅተን ማምረት በመጀመራችን ተጠቃሚ መሆን ችለናል፤ ምርትና ምርታማነታችንም እያደገ መጥቷል" ብለዋል።

አርሶ አደሮቹ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት አስፈላጊው ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው በመሆኑ በዘንድሮው የምርት ዘመን ከፍተኛ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026