የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስታዊ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

በአርባ ምንጭ ከተማ የተገነባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች የተለያዩ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ እያስቻለ ነው።

በክልሉም በወላይታ ሶዶ፣ በአርባ ምንጭ እና በዲላ ከተሞች ማዕከሉን ተደራሽ በማድረግ ህዝቡ ባለበት ሆኖ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኝ ለማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።


በዲጂታል ሥርአት ታግዞ የሚሰጠው አገልግሎት ለዘመናዊ የመንግስት አስተዳደር ጉልህ ፋይዳ አለው ያሉት አቶ ጥላሁን፣ አገልግሎቱ ፈጣንና ከሙስና የጸዳ በመሆኑ የዜጎችን እርካታ ከፍ ያደርገዋል ብለዋል።

ማዕከሉ ዜጎች ወደክልሉ የተለያዩ ከተሞች ሳይሄዱ የፌደራል ተቋማት አገልግሎቶችን ጭምር በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በክልሉ መንግስታዊ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ህዝብን ከወጪና እንግልት ለመታደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።

የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በበኩላቸው ማዕከሉ ሰው ተኮር እንደሆነና በመንግስት አገልግሎት ላይ ይታዩ የነበሩ ችግሮችን በመሠረታዊነት የሚፈታ ነው ብለዋል።


የተገልጋዩን ጊዜ፣ ጉልበት እና ወጪ የሚቀንስ መሆኑን ጠቅሰው፣ ውጤታማና ለዜጎች ክብር የሰጠ አገልግሎት በመሆኑ ህዝብና መንግስትን በማቀራረብ ለሀገሪቱ ብልጽግና ጉዞ ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል።

"መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መንግስት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል" ያሉት ደግሞ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ናቸው።


አገልግሎቱ በዲጂታል ሥርአት የታገዘ በመሆኑ ህዝቡን በፍትሃዊነት ለማገልገል፣ መረጃን በአግባቡ ለማደራጀት እንዲሁም የተገልጋይ እንግልትን ለማስቀረት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ413 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ መገንባቱን ገልጸዋል።


በማዕከሉ የምረቃ መርሀግብር ላይ በየደረጃው ካሉ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች በተጨማሪ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

ማዕከሉ አራት የፌደራልና አምስት የክልል ተቋማትን በአንድነት ያጣመረ ሲሆን ከ32 በላይ አገልግሎቶችም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው የሚሰጡበት መሆኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026