የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቆሻሻ አወጋገድና መልሶ አጠቃቀም ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳትና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ እያሳደጉ ነው

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በቆሻሻ አወጋገድ እና መልሶ ጥቅም ማዋል ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳት እና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ እያሳደጉ መሆኑን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።

በተጨማሪም ለከተማዋ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር በኩልም ጉልህ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተመላክቷል።

'ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ' የተሰኘ ዓለምአቀፍ ድርጅት ከአይኬኢኤ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር “የኢትዮጵያ አረንጓዴ መጻኢ ዕድል፦ በኢትዮጵያ የቆሻሻ አወጋገድ እና ሰርኩላር ኢንተርፕራይዞችን መገንባት” በሚል መሪ ሀሳብ ቆሻሻን ወደ ቢዝነስ ለመቀየር ያሰለጠናቸውን ሥራ ፈጣሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን አዲስ ሰልጣኞችም አቀባበል ተደረጎላቸዋል።


በምረቃ መርሃ-ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈጻሚ እሸቱ ለማ(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በከተማዋ ቆሻሻን ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲቀይሩ በማድረግ በኩል አበረታች ሥራ እየተሰራ ነው።

ይህም እንደ ሀገር በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

በቆሻሻ አወጋገድ እና መልሶ ጥቅም ማዋል ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳት እና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ ከማሳደግ ባሻገር ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር በኩል ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱም መሰል ስራ ፈጣሪዎችን እና የፈጠራ ሃሳቦችን በፖሊሲ፣ በማበረታቻ እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በማስተሳሰር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የ'ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ' ካንትሪ ዳይሬክተር መቅድም ጉልላት በበኩላቸው፤ ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር ቀጣይነት ያለው የፈጠራ ሥራ፣ ትብብር እና ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሥራ ፈጣሪዎች የአካባቢ ጥበቃ ተግዳሮቶችን የሚፈቱ ተግባራዊ መፍትሄዎችን በማዘጋጀትና ለማህበረሰቡ ሰፊ የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026