የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቆሻሻ አወጋገድና መልሶ አጠቃቀም ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳትና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ እያሳደጉ ነው

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በቆሻሻ አወጋገድ እና መልሶ ጥቅም ማዋል ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳት እና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ እያሳደጉ መሆኑን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።

በተጨማሪም ለከተማዋ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር በኩልም ጉልህ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተመላክቷል።

'ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ' የተሰኘ ዓለምአቀፍ ድርጅት ከአይኬኢኤ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር “የኢትዮጵያ አረንጓዴ መጻኢ ዕድል፦ በኢትዮጵያ የቆሻሻ አወጋገድ እና ሰርኩላር ኢንተርፕራይዞችን መገንባት” በሚል መሪ ሀሳብ ቆሻሻን ወደ ቢዝነስ ለመቀየር ያሰለጠናቸውን ሥራ ፈጣሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን አዲስ ሰልጣኞችም አቀባበል ተደረጎላቸዋል።


በምረቃ መርሃ-ግብሩ የተገኙት የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈጻሚ እሸቱ ለማ(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በከተማዋ ቆሻሻን ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲቀይሩ በማድረግ በኩል አበረታች ሥራ እየተሰራ ነው።

ይህም እንደ ሀገር በፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

በቆሻሻ አወጋገድ እና መልሶ ጥቅም ማዋል ላይ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የአዲስ አበባን የጽዳት እና የአረንጓዴ ልማት ደረጃ ከማሳደግ ባሻገር ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር በኩል ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱም መሰል ስራ ፈጣሪዎችን እና የፈጠራ ሃሳቦችን በፖሊሲ፣ በማበረታቻ እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በማስተሳሰር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የ'ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ' ካንትሪ ዳይሬክተር መቅድም ጉልላት በበኩላቸው፤ ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር ቀጣይነት ያለው የፈጠራ ሥራ፣ ትብብር እና ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሥራ ፈጣሪዎች የአካባቢ ጥበቃ ተግዳሮቶችን የሚፈቱ ተግባራዊ መፍትሄዎችን በማዘጋጀትና ለማህበረሰቡ ሰፊ የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026