የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው

Jun 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሰኔ 3/2018 (ኢዜአ)፦የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ኢትዮ - ቴሌኮም አስታወቀ።

"የኢትዮ ቴሌኮም እና የፍትህ ተቋማት ጥምረት ለዲጂታል ኢትዮጵያ ደህንነት" በሚል መሪ ሀሳብ በዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር እንዲሁም መሰረተ ልማት ላይ እየደረሰ ባለው ጉዳትና መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሊጋል ኦፊሰር አቶ ለማ ተሰማ፤ በቴሌኮም ዘርፍ የተገኘውን ስኬት ለማስቀጠል ኩባንያው የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ለተግባራዊነቱ እየተጋ ይገኛል ብለዋል።።

ባለፉት ዓመታት ተግባራዊ የሆኑት የቴሌኮም እና የዲጂታል አገልግሎቶች አካታች ሀገራዊ ልማትን በማፋጠን ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን አንስተው በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን ቀጣይ መዳረሻ እና ዲጂታል መፃዒ ዕድል የተሳካ ለማድረግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ በመቅረጽ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል።

አዲሱ ስትራቴጂ “አድማስ ዲጂታል” ኢትዮ ቴሌኮምን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እና በዲጂታል የጎለበተ ኩባንያ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸው ሀገራዊ የልማት አጀንዳዎችን በማፋጠን፣ በቀጣናውና በዓለም አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ አዳዲስ ዕድሎችን ለመክፈት ወሳኝ መሆኑንም አስረድተዋል።

በኩባንያው ያለፉት አመታት ስኬታማ ግስጋሴ ውስጥ የተለያዩ ተግዳሮቶች አጋጥመዋል ያሉት አቶ ለማ፤ በተለይም የዲጂታል ፋይናንስ እና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎችን ጠቅሰዋል።

በቴሌኮም መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም ዘረፋና ስርቆትም ሌላኛው ችግር መሆኑን አንስተው እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከል በተለይም ከፍትህ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።


በኢትዮ ቴሌኮም የሕግ ጉዳዮች አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ታየ፤ የስልጠና መድረኩ ያተኮረው በዲጂታል ፋይናንስ ላይ የሚፈጸም ወንጀል፣ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል እንዲሁም የቴሌኮም መሠረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ወንጀልን ለመከላከል ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

በሀገሪቷ የዲጂታል ፋይናንስና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀልን ለመከላከል ከፍትህና የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ ከፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ፣ ከፖሊስና ፍርድ ቤቶች የተውጣጡ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026