የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ በመኸር ወቅት ከ264 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ይለማል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አፍጥር፣ ሰኔ 5/2018 (ኢዜአ):-በጉራጌ ዞን በተያዘው የመኸር ወቅት ከ264 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የዞኑ የ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የሰብል ልማት ንቅናቄ መድረክ ''የተቀናጀ ግብርና ለቤተሰብ ብልፅግና'' በሚል መሪ ሃሳብ በቸሃ ወረዳ ተካሂዷል፡፡


የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በበኩላቸው በዚህ ወቅት እንዳሉት በዞኑ በመኸር እርሻ ከ264 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል።

ለመኸር እርሻ ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ እየቀረበ መሆኑን ጠቁመው፣ 56 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በመጠባበቂያነት መያዙንም ተናግረዋል፡፡

በመኸር ወቅቱ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ቦለቄ፣ የቢራ ገብስ እና ሌሎች ሰብሎች እንደሚለሙ ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅትም የእርሻ ስራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡

እንደ አቶ አበራ ገለጻ በመኸሩ ከሚለማው አጠቃላይ መሬት ውስጥ 41ሺህ 800 ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ ነው።


የቸሃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ድንቁ በበኩላቸው እንዳሉት በዓመት ከሦስት ጊዜ በላይ ለማምረት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋቱ በግብርና ምርት ላይ ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው።

የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በወቅቱ ከማሰራጨት ባለፈ የአርሶ አደሩን ፍላጎት እና አቅም በሚገባ በመለየት በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በተፋሰስ የለሙ አካባቢዎች ጭምር በተለያዩ ሰብሎች እየለሙ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የጌታ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሙዘፋ የሱፍ ናቸው።

የወረዳው አርሶ አደሮች በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ገቢ የሚያስገኙ ምርቶች ላይ እንዲያተኩሩ በመደረጉ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ህይወታቸውን እየቀየሩ መጥተዋል ብለዋል።

በንቅናቄ መድረኩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በዞኑ በሌማት ትሩፋት በተከናወኑ የዶሮ እርባታ፣ የወተት እና የእንስሳት ልማት ስራዎች እንዲሁም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።


በሰብል ልማትም ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ያሉት አስተዳዳሪው በተያዘው የመኸር እርሻ አንድም መሬት ጾም እንዳያድር ልማቱን ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

በበልግ ወቅት በዝናብ ስርጭት መዘግየት ምክንያት የጠፋውን የበቆሎ ሰብልን ለማካካስ አስፈላጊው የግብርና ግብዓት በመጠቀምና የተሻሻሉ አሰራሮችን በመተግበር ይሰራል ሲሉም አክለዋል።

በመድረኩ የተለያዩ ወረዳዎች እና ከተማ አመራሮች፣ የግብርና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026