የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀን ከ250 ሲሊንደር በላይ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት ከራሱ አልፎ ለአካባቢ የህክምና ተቋማት ማቅረብ ጀምሯል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀን ከ250 ሲሊንደር በላይ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት ከራሱ አልፎ ለአካባቢ የህክምና ተቋማት ማቅረብ መጀመሩን ገለጸ፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመትና የማስተማሪያ ሆስፒታሉን 100ኛ ዓመት ባለፈው ዓመት ማክበሩ ይታወሳል፡፡

በዚህም ዩኒቨርሲቲው የተቋቋመበትን የማህበረሰቡን ችግር ፈች አገልግሎት የመስጠት ዓላማ ታሳቢ በማድረግ ከ20 በላይ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል፡፡

የጨረር ሕክምና ማዕከል፣ የሕክምና ኦክስጅን ማምረቻ፣ ዘመናዊ የደረቅና እርጥብ ቆሻሻ ማስወገጃና ሌሎችም ማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክቶች በምርምር ተቋቁመው ገቢራዊ ተደርገዋል፡፡

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምህንድሥና ሥራ አገልግሎት ዳይሬክተር እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ወንደወሰን በየነ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ታካሚዎች ሕክምና የሚያገኙት ከአዲስ አበባ ተገዝቶ በሚመጣ የሕክምና ኦክስጅን ነበር፡፡

በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ በቀን 250 ሲሊንደር እና ለ600 የህሙማን አልጋዎች በቀጥታ የሚደርስ የሕክምና ኦክስጅን በማምረት እጥረቱን ሙሉ በሙሉ መፍታት ችሏል ብለዋል፡፡

የሕክምና ኦክስጅን ማዕከሉ ኦክስጅን ለማምረትየተፈጥሮን አየርን በማጣራት ጥቅም ላይ እንደሚያውል ገልጸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከራሱ አልፎ ለአካባቢው የሕክምና ተቋማት የሕክምና ኦክስጅን እያቀረበ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ አድማሱን በማስፋት ምርቱን የማሳደግና ገቢ የማመንጨት እቅድ ይዟል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026