የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የፌዴሬሽኑን አሰራርና መረጃ አያያዝ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመንና በጋራ ለመስራት የሚያስችል የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራርመዋል።


የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ፌደሬሽኑ ዘመናዊ የምዝገባ ሥርዓትን በመዘርጋትና ተቋሙን ዲጂታላይዝ በማድረግ ረገድ ብዙ መሥራት እንደሚገባ አመልክተዋል።


በስምምነቱ መሰረት በቴክኖሎጂ የዳበረ ተቋም ለመገንባት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል።


ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ፈጣንና ቀልጣፋ የአትሌቶች አገልግሎት ለመስጠት በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።


የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የኢንፎርሜሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃኒባል ለማ፤ አትሌቲክስ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ያኮራ ታላቅ ዘርፍ መሆኑን ገልጸዋል።


የፌዴሬሽኑ የዲጂታል ሉዓላዊነት (Digital Sovereignty ) ለማጠናከር ፣ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረው የሚያስችል የቴክኖሎጂ ትስስርን ጨምሮ አስፈላጊው ሁሉ ለማድረግ ተቋማቸው ለአትሌቲክሱ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል።


ስምምነቱ ከስልጠና ማዕከላት ጀምሮ ፕሮጀክቶችን፣ ክለቦችን እና ተቋማትን ያቀፈ የአትሌቶች ምዝገባ ሥርዓትን የሚዘረጋ ሲሆን፤ የውድድሮችን የአደረጃጀትና የአመራር (ማኔጅመንት) ሥርዓት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።


ከአትሌቶች አገልግሎት ጋር የተያያዙ የኤምባሲ ጉዳዮችን ከእጅ-በእጅ (ማኑዋል) አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የሚቀይር በመሆኑ፣ ይደርስ የነበረውን እንግልት እንደሚያስቀርም ፌዴሬሽኑ ገልጿል።


በተጨማሪም ስምምነቱ የፋይናንስ፣ የንብረት አስተዳደር እና የግዥ ሥርዓቶችን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ የፌዴሬሽኑን ድረ-ገጽ (ዌብሳይት) ማበልጸግን ጨምሮ በርካታ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎችን የሚያካትት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026