የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዘንድሮ በጀት አመት ከ7 ሺ 7መቶ በላይ የገጠር ቤተሰቦች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ተሸጋግረዋል

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፣ ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፡- በዘንድሮ በጀት አመት ከ 7 ሺህ 7 መቶ በላይ የገጠር ቤተሰቦች ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።

ተረጂነትን የሚጠየፍ አምራች ማህበረሰብ የማፍራትና በዘርፉ ለተገኙ ውጤቶች እውቅና የመስጠት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ነው የተገለፀው።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሚስራ አብደላ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ ዝናብ አጠር በሆነው በድሬደዋ ገጠራማ አካባቢዎች ማህበረሰቡ ከጠባቂነትና ከተረጂነት ወጥቶ ምርታማ እንዲሆን በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።

ባለፉት አምስት አመታትም በአነስተኛ መስኖ፣ በሌማት ትሩፋት፣ በሰብልና በፍራፍሬ እንዲሁም በተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ የተከናወኑ ተግባራት ህብረተሰቡን ከገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ወደ አምራችነት አሸጋግሯል ብለዋል።

በተለይም የገጠሩን ክላስተር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተከናወኑት ተግባራት ተረጂነት የሚጠየፍ ትውልድ በማፍራት ውጤት እንዲመዘገብበት አድርጓል ነው ያሉት።

አርብቶ አደሩ እና አርሶ አደሩ ማሕበረሰብ በተፈጥሮ ሃብቱና በተገነቡት መሰረተ ልማቶች በመታገዝ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያደርገውን ጉዞ ለማሳለጥ እንዳስቻለም ነው የተናገሩት።

ለአብነትም ኡሉል ሞጆ የገጠር ቀበሌ ህብረተሰብ ሙሉ በሙሉ ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገሩንም ነው ኃላፊዋ ያነሱት።

በዘንድሮው በጀት ዓመትም 7 ሺህ 7መቶ በላይ የገጠር ቤተሰብ ከተረጂነት ወደ አምራችነት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል ።

በግብርና፣ በአነስተኛ የንግድ ስራዎች ሽግግር ላደረጉት አርሶ እና አርብቶ አደሮች ለስራቸው መቀላጠፍ የመነሻ ካፒታልና ሙያዊ ድጋፍ መደረጉንም አንስተዋል።

ከተረጂነት ለተሸጋገሩት የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ ወር መጨረሻ ዕውቅናና ሽልማት እንደሚሰጥም ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026