🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የድህነትና ኋላቀርነት ታሪክን በሚሰብር የመነሳትና የብልፅግና የእጥፋት ዘመን ላይ ናት ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ሀገራት ከችግርና ጉስቁልና የሚሻገሩበት የእጥፋት ጊዜ አለ።
ኢትዮጵያ ያለችበት ዘመን የእጥፋት፣ ብልፅግናና የመነሳት ዘመን መሆኑንም ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ በመንግስት መሪነት፣ በግል ባለሀብቱ ተሳትፎና ትብብር የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
የሀዋሳ የልማት ፕሮጀክት ትልቅ በጀት የሚጠይቅ፤ ሲጠናቀቅም ለነገ ተጠቃሚነት ማረጋገጫ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በሁሉም አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።
አንድነታችንን እንደጋሻና ጦር በመጠቀም ኢትዮጵያን ከድህነትና ኋላቀርነት የምናላቅቅበትና በጋራ የምናለማበት መጪው ጊዜ ብሩህ ነው ብለዋል።
መድረኩ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ይሁንታ አግኝቶ በተመረጠበትና ለመንግስት ምስረታ እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት መዘጋጀቱ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ነው ብለዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026