🔇Unmute
ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የቡታጅራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችሉ አሰራሮችን የማጠናከር ሥራ በትኩረት ይከናወናል፡፡
በዚህም የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በማቅረብ መስጠት የሚያስችለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።
የክልሉ መንግስት ከማህበረሰቡ ለሚነሱ የልማት፣ የፍትሀዊ ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ለማቀላጠፍ የሚያግዙ ማዕከላትን ከማስፋት ባለፈ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው የማዕከሉ ሥራ መጀመር ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል።
በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶች መሰጠቱም የማህበረሰቡን እንግልት ከማስቀረት በተጨማሪ የተጠያቂነት ስርዓትን በማስፈን ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ እንደገለጹት፣ በከተማው ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ210 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል።
ማዕከሉ የመንግስትን አገልግሎት በማዘመን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡
በማዕከሉ የስድስት ተቋማት 22 አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንደሚደረጉም ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ የክልሉ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞንና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 7, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...
Jul 3, 2026
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026