የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ተግባራት እንደሚጠናከሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የቡታጅራ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችን መፍታት የሚያስችሉ አሰራሮችን የማጠናከር ሥራ በትኩረት ይከናወናል፡፡

በዚህም የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በማቅረብ መስጠት የሚያስችለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።

የክልሉ መንግስት ከማህበረሰቡ ለሚነሱ የልማት፣ የፍትሀዊ ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን ለማቀላጠፍ የሚያግዙ ማዕከላትን ከማስፋት ባለፈ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን በበኩላቸው የማዕከሉ ሥራ መጀመር ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል።

በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶች መሰጠቱም የማህበረሰቡን እንግልት ከማስቀረት በተጨማሪ የተጠያቂነት ስርዓትን በማስፈን ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ እንደገለጹት፣ በከተማው ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ210 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል።

ማዕከሉ የመንግስትን አገልግሎት በማዘመን በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡

በማዕከሉ የስድስት ተቋማት 22 አገልግሎቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንደሚደረጉም ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ የክልሉ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞንና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026